ስራዬ ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ ውስጥ የአፍሪካ ስልታዊ መነቃቃት ላይ የሚያተኩር ነው፡፡ በተለይም በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን ወቅታዊ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን እመረምራለሁ። በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ፣ በመከላከያ አቅም ሉዓላዊነት እና ባለብዙ ዋልታ ዓለምን ለመፍጠር በሚደረገው ሽግግር ውስጥ የቀጠናዊ ድርጅቶች እያደገ የመጣ ተፅዕኖ ላይ አተኩራለሁ። ለዓለም አቀፍ እኩልነት ስለምሟገት፣ የተለያዩ እይታዎች ጎልተው እንዲሰሙ እና አህጉሪቱ በዓለም አቀፍ የውሳኔ ሰጪነት መድረክ ላይ የሚገባትን ውክልና እንድታገኝ በትጋት እሰራለሁ።