- Sputnik አፍሪካ, 1920
Turning Africa Forward
በአህጉሪቱ ስልታዊ መነቃቃት ላይ ግልጽ እይታን የሚሰጥ በስፑትኒክ አፍሪካ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ፕሮግራም ። ከዜናዎች ባሻገር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን እየተለወጠ የመጣ ሚና በጥልቀት ይተነትናል፤ የወደፊቱን የዓለም ሥርዓት በመቅረጽ ረገድ ያለውን አቅጣጫ በሰፊው ይዳስሳል።

የአፍሪካ የአየር ክልል ነፃነት እና የውሃ ስነ-ምህዳር መዋቅራዊ ሉዓላዊነት

የአፍሪካ የአየር ክልል ነፃነት እና የውሃ ስነ-ምህዳር መዋቅራዊ ሉዓላዊነት
ሰብስክራይብ
''አፍሪካ የአየር ክልሏን፣ የንግድ ፍሰቷን እና የመንገደኞች እንቅስቃሴን በራሷ እጅ በማስገባት መዋቅራዊ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ አለባት'' ሲሉ የአቪዬሽን ተንታኝ ደሪክ ንሴኮ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት እ.ኤ.አ ከሰኔ 15 አእስከ ሰኔ 19 ፣ 2026 በቶጎ ሌሜ የሚካሄደው የአፍሪካ አየር ትራንስፖርት ኮንቬንሽን እና ኤክስፖ ለአህጉሪቱ የተዋሃደ የአየር ክልል (SAATM) መፈጠር ምን ዓይነት ተግባራዊ ዕድሎችን ይዞ ይመጣል? የአየር ትኬት ዋጋንና ቀረጥን በመቀነስ ረገድስ ምን ሚና አለው? ስንል ከአቪዬሽን ተንታኝ እና የኤር ስፔስ አፍሪካ መስራች ደሪክ ንሴኮ ጋር ሰፊ ቆይታን አድርገናል። በክፍል ሁለት ደግሞ፣ የአፍሪካን የውሃ ሀብትና ስነ-ምህዳር ከኬሚካል ብክለት ለመጠበቅ የምዕራባውያንን የተጽዕኖ ሞዴሎች በመተው፣ የደቡብ-ለደቡብ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የምርምር ትብብሮች ለአህጉሪቱ ሉዓላዊነት ስላላቸው ወሳኝ ጠቀሜታ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ጤና ቶክሲኮሎጂ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶ/ር ሰብለወርቅ መኮንን ሸገን ጋር በጥልቀት ተወያይተናል።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ይከታተሉ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0