- Sputnik አፍሪካ, 1920
Turning Africa Forward
በአህጉሪቱ ስልታዊ መነቃቃት ላይ ግልጽ እይታን የሚሰጥ በስፑትኒክ አፍሪካ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ፕሮግራም ። ከዜናዎች ባሻገር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን እየተለወጠ የመጣ ሚና በጥልቀት ይተነትናል፤ የወደፊቱን የዓለም ሥርዓት በመቅረጽ ረገድ ያለውን አቅጣጫ በሰፊው ይዳስሳል።

የዓለም አቀፉ የፍትህ ሥርዓት መዛባትና የአፍሪካ ዲጂታል ዘርፍ ህልውና

የዓለም አቀፉ የፍትህ ሥርዓት መዛባትና የአፍሪካ ዲጂታል ዘርፍ ህልውና
ሰብስክራይብ
''ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) የተቋቋመው በአፍሪካውያንና ምራባውያኑ ‘አፈንጋጭ’ በሚሏቸው ሀገራት ላይ እርምጃ ለመውሰድ ብቻ ነው። ምዕራባውያንን ኢላማ ሲያደርግ ግን ሕጉ በድንገት ይወገዛል። ሲሉ የሕግ ምሁርና ፓን-አፍሪካኒስት ፕ/ር ፒ.ኤል.ኦ ሉሙምባ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በመጀመሪያው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት በክፍል አንድ ዓለም አቀፍ ሕጎችና እንደ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ያሉ ተቋማት ለምዕራባውያን ፍላጎት እንዴት መሣሪያ እየሆኑ እንደሆነ እንዲሁም አፍሪካ ዲጂታል ቅኝ ግዛትን ለመከላከል መውሰድ ስላለባት እርምጃዎች ከታዋቂው የሕግ ምሁርና ፓን-አፍሪካኒስት ፕ/ር ፒ.ኤል.ኦ ሉሙምባ ጋር ሰፋ ያለ ቆይታ አድርገናል።
በክፍል ሁለት ደግሞ “የዲጂታል ከለላ፡ የኢትዮጵያ የሳይበር ሉዓላዊነት መንገድ” በሚል ርዕስ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የግል የሳይበር ደህንነት ኩባንያ (ZSecuredTech) መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ከሆኑት አቶ ፋሪስ ሙባረክ ጋር ተወያይተናል።
ሙሉውን መረጃ ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
አዳዲስ ዜናዎች
0