- Sputnik አፍሪካ, 1920
Turning Africa Forward
በአህጉሪቱ ስልታዊ መነቃቃት ላይ ግልጽ እይታን የሚሰጥ በስፑትኒክ አፍሪካ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ፕሮግራም ። ከዜናዎች ባሻገር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን እየተለወጠ የመጣ ሚና በጥልቀት ይተነትናል፤ የወደፊቱን የዓለም ሥርዓት በመቅረጽ ረገድ ያለውን አቅጣጫ በሰፊው ይዳስሳል።

የ2026 የዓለም ዋንጫ ፡ የቲኬት ዋጋ መናር እና ጂኦፖለቲካ የጋረዱት ተወዳጁ ስፖርት

የ2026 የዓለም ዋንጫ፡-የቲኬት ዋጋ መናር እና ጂኦፖለቲካ የጋረዱት ተወዳጁ ስፖርት
ሰብስክራይብ
''አሁን ላይ እንደ ስፖርት ባለሙያ መነጋገር ያለብን 'የትኛው ተጫዋች በዚህ አለም ዋንጫ ላይ ሊጎላ ይችላል? ሊዮኔል ሜሲ ምናልባትም በደመቀ ሁኔታ እግር ኳስን እንዴት ይሰናበታል? በሚሉ ውብ ስፖርታዊ እሳቤዎች ላይ ነበረ ። ነገር ግን አሁን ላይ መገናኛ ብዙሃኑን የሞላው የትኬቶችና የአኮሞዴሽን ዋጋ መወደድ እና ከሜዳ ውጪ ያሉ የንግድና የጂኦፖለቲካ ጉዳዮች ናቸው ። ይህ ዳይናሚክ ፕራይሲንግ (እየተለዋወጠ የሚንር የዋጋ ተመን) የትኬት ክፍያ ሁኔታ ውድድሩን ለተርታው ደጋፊ እጅግ አስቸጋሪ አድርጎታል'' ሲል የስፖርት ጋዜጠኛው እስከአድማስ ሙላቱ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል።
በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስታችን፤ የመጀመሪያው ጉዳይ የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ለአፍሪካ ተጨማሪ የተሳትፎ ቦታዎችን በመስጠት ትልቅ ዕድል ይዞ መጥቷል ቢባልም፣ ደጋፊዎቿ ግን በኢኮኖሚ ጫና ወደ እየተገፉ መሆናቸውን በመገንዘብ ይህ ነገር ለአፍሪካውያን ስጦታ ነው ወይስ የንግድ ማጧጧፊያ? ስንል የስፖርት ጋዜጠኛውን እስከአድማስ ሙላቱን በስልክ አነጋግረን በጥልቀት ፈትሽነዋል ።
በመቀጠል ደግሞ ኢትዮጵያ፣ ከከፍተኛ የነዳጅ ወጪና ጥገኝነት ለመላቀቅና በራስ ታዳሽ ኃይል ለመቆም ያወጣችውን አዲስ መመሪያ እንቃኛለን። በሀገሪቱ ያሉ የመኪና መገጣጠሚያ ተቋማት በሙሉ ትኩረታቸውን ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ብቻ እንዲያዘነብሉ ስለሚያደርገው ፍኖተ ካርታ፣ ስለ መሰረተ ልማት ዝግጅቶች እና የኢንዱስትሪ ነፃነት ዙሪያ ከትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ ከአቶ አሰፋ ሐዲስ ጋር ፍሬያማ ቆይታ አድርገናል ።
ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0