አፍሪካ በምዕራቡ ዓለም መገናኛ ብዙሀን ጠባብ ፣ ከመጠን በላይ ተስፋ አስቆራጭ እና ጨለምተኛ አህጉር ተደርጋ ትሳላለች። አቅራቢው እንደ አንድ አፍሪካዊ ጋዜጠኛ የአፍሪካን ብሩህ መልኮች በልክ ያዉቃል፡፡ እናም አህጉሪቱ የራሷን ታሪክ በራሷ አንደበት መናገር መቻል አለባት ብሎ ያምናል። ለዚያም የአፍሪካን ድምፅ ማጉላት፣ በጎ ገፅታዎቿንም ማሳየት ተልዕኮዉ አድርጎ የአፍሪካን ጥበብ ፣ ታሪክ ስልጣኔ ከፖለቲካ ፣ ኢኮኖሚ እና ሌሎች ማህበራዊ መልኮች ጋር እያዋሃደ የተለያዩ ዝግጅቶችን ወደ እናንተ ያቀርባል።