- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል።አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

የጥቁር ህዝቦች የካሳና ፍትህ ጉዳይ ፦ አውሮፓዉያኑ እንዲነሳ የማይፈልጉት ጥያቄ ለምን ሆነ ?

የጥቁር ህዝቦች የካሳና ፍትህ ጉዳይ ፦ አውሮፓዉያኑ እንዲነሳ የማይፈልጉት ጥያቄ ለምን ሆነ ?
ሰብስክራይብ
"ብዙዎቻችን ከየት እንደመጣን ምንም ባናውቅም፣ ስደተኞች ግን አይደለንም። በእገታ የተወሰድን አፍሪቃውያን ነን። አያት ቅድመ አያቶቻችን ማንነታቸዉን ሳያውቁ ወደ መቃብር ወርደዋል። የ'ባሪያ' ልጆች መሆናችንን ብቻ ነው የተማርነው። ይህም ለሕዝባችን ብዙ ግራ መጋባት ፈጥሯል፣ የማንነት እጦትን ፈጠሯል" ሲሉ ጸሐፊ እና የፓንአፍሪካኒዝም አቀንቃኟ ጅኔል ሆይሌት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ጥንቅራችን፣ የአፍሪካን የቅኝ ግዛት በደልና ፍትህ እንዲሁም የካሳ ጥያቄን እናነሳለን፡፡ ይሄው ጥያቄ በአውሮፓውያን ዘንድ ከመውያያ አጀንዳነት ለምን እንደሚገፋና ሌሎችንም ጉዳዮችን መነሻ አድርገን ጸሐፊ እና የፓንአፍሪካኒዝም አቀንቃኝ ጅኔል ሆይሌት ጋር በሰፊው እንወያያለን። በሁለተኛው ጥንቅራችን ደግሞ አፍሪካ ከሕገ መንግሥታዊነት፣ ከዳኝነት ነፃነት ጋር በተያያዘ ያላትን ቀጣይ ትግል እና በዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት ዙሪያ ስላለው ሰፊ ክርክር እንመለከታለን። ጌታቸው አሰፋ (ዶ/ር) ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ተባባሪ ፕሮፌሰር እና አቶ ቸርነት ሆርዶፋ፣ የአፍሪካ ሕገ መንግሥታዊ ዳኝነት ኮንፈረንስ አባልን አነጋግረናል።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerAfripods Spotify Pocket Casts Podcast Addict CastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0