- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል።አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

ድርብ መስፈርት፡- የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት እና የአፍሪካ የፍትህ ጥያቄ

ድርብ መስፈርት፡- የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት እና የአፍሪካ የፍትህ ጥያቄ
ሰብስክራይብ

‘‘ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት በሶሪያ ፣ ኢራቅና አፍጋኒስታን ውስጥ የተፈጸሙ ወንጀሎች፣ በብሪታኒያ በተፈጸሙ ወንጀሎች ዙሪያ ተጀምረው የነበሩ ምርመራዎች በአሜሪካ ጣልቃ ገብነት በድንገት እንዲቋረጡ ሆነዋል፡፡ ለምን ብለህ ብትጠይቃቸው ግን አሳማኝ ምክንያት አይሰጡህም፡፡ ተመሳሳይ ነገሮችን በተለያየ መንገድ የሚዳኝበት መንገድ በጣም የገዘፈ ነው፡፡’’ ሲሉ ኢትዮጵያዊው የህግ ባለሙያና ጠበቃ አንዷለም በእውቀቱ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

የዛሬው ድረም ኦፍ ቼንጅስ ዝግጅታችን በሁለት ጉዳዮች ላይ እንወያያለን፡፡ በቀዳሚነት አፍሪካን ማጥቂያ የሆነው በዓለምአቀፉ ወንጀለኞች ፍርድቤት የሚደርስባት አድሏዊ አሰራርና በደልን እንዳስሳለን። ለዚህም የህግ ባለሙያና ጠበቃ አንዷለም በእውቀቱ አብረዉን ቆይታ ያደርጋሉ። በሁለተኛው ጥንቅራችን ደግሞ የአፍሪካ ደራሲያን እና አሳታሚዎች የአህጉሪቱ የባህልና የቋንቋ ሀብቶች ተገቢ እና እውነተኛ እውቅና ያገኙ ዘንድ በአለም አቀፍ መድረኮች ስለሚያሰሟቸው ጥሪዎች እንወያያለን ፤ በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ስነጽሁፍ መምህር እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የማህበራዊ ሳይንስ እና ስነሰብ ኮሌጅ ዲን አስቻለው ለገሰ (ዶ/ር) ጋር ቆይታ አድርገናል።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezerAfripods Spotify Pocket Casts Podcast Addict CastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0