- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል።አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

ከትናንት እስከ ዛሬ ፡ የዓለምአቀፍ ተቋማት አድሏዊነትና የፍትሐዊነት ጥያቄ ከሊግ ኦፍ ኔሽን እስከ ጸጥታው ም/ቤት

ከትናንት እስከ ዛሬ ፡ የዓለምአቀፍ ተቋማት አድሏዊነትና የፍትሐዊነት ጥያቄ ከሊግ ኦፍ ኔሽን እስከ ጸጥታው ም/ቤት
ሰብስክራይብ

"አፍሪካ እንደገና የተዋቀረ፣ ገለልተኛ፣ ተጠያቂነት የሰፈነበት ዓለም አቀፍ ስረዐት ያስፈልጋታል። የተባበሩት መንግስታት አሁን ባለው አቋም የአፍሪካን ጥቅም የሚያስከብር አይደለም። በእኔ እይታ የተባበሩት መንግስታት፣ በዩናይትድ ስቴትስ የሚጋለብ፣ምዕራባውያን የሚነዱት ፈረስ ነው።" - ሲሉ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና አለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ የሆኑት አቶ ዳዊት መዝገበ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ጥንቅራችን ፣ በቀዳሚነት አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት እና ሌሎች አለም አቀፍ ተቋመት ውስጥ ፍትሃዊ እና እኩል ውክልና ለማግኘት የምታደርገውን ቀጣይነት ያለው ጥረት እንፈትሻለን። ለዚህም በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እን አለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ የሂኑትም አቶ ዳዊት መዝገበን አነጋግረናል። በሁለተኛው ጥንቅራንም ኃይማኖታዊ እና ባህላዊ ትውፊቶችን ጠብቆ ማቆየት ለአፍሪካ፣ ብሎም ኢትዮጵያ እንደ ሩሲያ ካሉ አገራት ጋር ለሚኖራት መልካም ግንኙነት ስለሚኖራቸው ቦታ ደግሞ ሁለተኛው ጥንቅራችን ያስቀኛናል። በዚህ ጉዳይ ያላቸውን ሃሳብ እንዲያጋሩን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የጥናት እና ምርምር ዳይሬክተር የሆኑትን መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤልን አነጋግረናል።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
አዳዲስ ዜናዎች
0