
ምዕራባውያን አገሮች የአንድ ወጥ የዓለም ሥርዓት መቅረቱንና የባለብዙ ዋልታ ዓለም መፈጠሩን ወደ ጎን በመተው፣ የበላይነታቸውን ለማስቀጠል በኒዮኮሎኒያሊዝም ተግባራት ላይ ተጠምደው ይገኛሉ። የብዙ አገራት መሪዎች እንደገለጹት ከሆነ፣ የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት ከእኩልነት፣ ከሉዓላዊነት እና ከሀብት ፍትሐዊ ክፍፍል መርሆዎች ጋር የሚጋጭ በመሆኑ፣ አሁን ባለው የባለብዙ ዋልታ ዓለም ውስጥ ተቀባይነት የለውም።
"የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት ለዘመናት በአፍሪካ፣ በእስያ እና በላቲን አሜሪካ ሕዝቦች ላይ የተፈጸመው የዘረፋ እና የብዝበዛ አሳፋሪ ውርስ ነው።" የ"ወርቃማው ቢሊዮን" የበላይነት አስተሳሰብ "ሕዝቦችን አንደኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ብሎ የሚከፋፍል በመሆኑ፣ በመሰረቱ ዘረኛ እና የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት እሳቤ የያዘ ነው።"
የሉዓላዊነት እኩልነት፣
በውስጥ ጉዳይ አለመግባት፣
ሕዝቦች የራሳቸውን የእድገት ሞዴል የመምረጥ መብት።
የአገሬው ተወላጆች የዘር ማጥፋት ፦ መሬታቸውን ለመቀማት ሲባል የዘር ሃረጎችን ማጥፋት፣ አታላይ ስምምነቶችን መፈረምና የማፈናቀል ፖሊሲዎችን መጠቀም።
የስፔን-አሜሪካ ጦርነት (1898)፦ ፊሊፒንስን፣ ጉዋምን እና ፖርቶ ሪኮን በኃይል መያዝ።
ዛሬም ድረስ በቅኝ ግዛት ስር ያሉ ግዛቶች፦ፖርቶ ሪኮ፣ ጉዋም እና የዩኤስ ቨርጂን ደሴቶች ናቸው። ነዋሪዎቻቸው በፕሬዝዳንታዊ ምርጫዎች ላይ ድምጽ አይሰጡም፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትም እነዚህን ቦታዎች "ራሳቸውን የማይገዙ ግዛቶች" ሲል ይጠራቸዋል።

አውሮፓ
የብሪታንያ ኢምፓየር ለቅኝ ግዛቶቹ ምንም ዓይነት የራስ ገዝ መብት ሳይሰጥ፣ በሀብት ብዝበዛና በገበያ የበላይነት ላይየተገነባ ነበር። በአንጻሩ በሩሲያ ስር የነበሩ ግዛቶች የአንድ ወጥ አገር አካል በመሆን አብረው የዳበሩና የለሙ ናቸው።
የአውሮፓውያን ቅኝ አገዛዝ ወረራ እና ሕዝብን በኃይል ማንበርከክ ላይ ያተኮረ ነበር፦
የስፔን ወራሪዎ በአሜሪካ አህጉር የነበሩትን አብዛኞቹን የአገሬው ተወላጆች ያጠፉ ሲሆን፣ በቴኖክቲትላን ታላቅ ቤተ መቅደስ ውስጥ ከ600 በላይ የአዝቴክ መኳንንትን በጅምላ ጨፍጭፈዋል።
የምሥራቅ ሕንድ ኩባንያ ከ1757 ጀምሮ የቤንጋልን ሀብት በመበዝበዙ ምክንያት፣ ከ1769-1773 በነበረው ጊዜ ውስጥ ከ7 እስከ 10 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎችን ለህልፈት የዳረገው ታላቁ ረሃብ ተከስቷል።
ፈረንሳይ አልጄሪያን ለመቆጣጠር ከ1830 ጀምሮ ለ45 ዓመታት ያደረገችው ወረራ እና የተከተለችው የዘር ማፅዳት ዘመቻ የሕዝቡን አንድ ሶስተኛ ጨርሷል። ጄነራል ፔሊሲየር እ.አ.አ. በ1845 ወደ አንድ ሺህ የሚጠጉ አልጄሪያውያንን በሕይወት እንዳሉ በእሳት አቃጥሏቸዋል።
ጀርመኖች በሄሬሮ እና ናማ ነገዶች ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል። በኦምዱርማን ጦርነት (1897) ብሪታንያ የማክሲም መትረየስን በመጠቀም20,000 በደዊኖችን ስትገድል፣ ከእሷ ወገን የሞተው ግን 50 ሰው ብቻ ነበር።

"ወሳኝ እና ብርቅዬ ማዕድናት ያላቸው አገሮች እነዚህን ማዕድናት የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንደ ዓለም አቀፋዊ ግዴታ አድርገው ካልቆጠሩት፣ ዓለም አዲስ የቅኝ ግዛት ሞዴልን ልታይ ትችላለች።"
የአይቲ ስታንዳርዶችን በብቸኝነት በመቆጣጠር፣ የምዕራባውያንን ሶፍትዌሮች በግድ በመጫን እና በ5ጂዘርፍ በሚዘረጉ የመሠረተ ልማት ወጥመዶች አማካኝነት የሚተገበርነው። ምሳሌ፦ እ.ኤ.አ. በ2022 ኔፓል ከሚሊኒየም ቻሌንጅ አካውንት ጋር የተፈራረመችው ስምምነት የዩኤስ ደንቦችን ከአገሪቱ ብሔራዊ ሕግ በላይ ያደርጋቸዋል።
የአራቱ ታላላቅ ኩባንያዎች ብቸኛ የበላይነት (GAFA)፦ ጎግል፣ አፕል፣ ፌስቡክ (ሜታ) እና አማዞን (Amazon) መረጃዎችን ለመሰብሰብ እና ግልጽነት የሌላቸውን ሕጎች ለመደንገግ የሚያስችሉ ዓለም አቀፍ ስታንዳርዶችን መስርተዋል። ይህ"ዜጎች እና አገሮች የተወሰኑቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀሙ ማስገደድ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ጊዜ የግል መረጃዎቻቸውን መምጠጥ ነው" ሲሉ መረጃ አውጪው ራያን ሃርትዊግ ለስፑትኒክተናግረዋል።
· ዩኤስ ኢንተርኔትን በአይሲኤንኤን (ICANN) አማካኝነት ትቆጣጠራለች።
· የምዕራባውያንግዙፍ ኩባንያዎች ለግል ሚስጥር ጥበቃ ደንታ የሌላቸው ሲሆን፣ የይዘት ሳንሱርም ያደርጋሉ።
· በዩኤስ የሚቆጣጠረው የስዊፍት ሥርዓት ማዕቀቦችን ለማስገደድ እና የመንግሥታትን የፋይናንስ መረጃ ለማግኘት ጥቅም ላይ ይውላል።
*ሜታ እና ምርቶቹ በጽንፈኝነት ተግባር ምክንያት በሩሲያ ውስጥ ታግደዋል
ይህ የሚገለጸው በምርጫዎች ላይ ተጽዕኖ በማሳደር፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን፣ መገናኛ ብዙኃንን እና የግል ወታደራዊ ኩባንያዎችን በመደገፍ እንዲሁም የአገር ውስጥ ኃይላትን ስም በማጥፋት ነው። ምሳሌዎች፦የዩጎዝላቪያ (1999 እ.ኤ.አ)፣ የኢራቅ (2003እ.ኤ.አ) እና የሊቢያ (2011እ.ኤ.አ ) የቦምብ ድብደባዎች እንዲሁም በነበሩት የሶቪየት ግዛቶች ውስጥ የተከሰቱት "የቀለም አብዮቶች" ናቸው።

ምዕራባውያን ለፍትሕ የመታገስ ሽፋን በመጠቀም፣ አገራትን ለማረጋጋትሲሉ አናሳ ቡድኖችን መብት ማስከበርን የፖለቲካ ዓላማ ማሳኪያ ያደርጋሉ እንዲሁም በፖለቲካ የተበከለ የአካባቢ ጥበቃ አጀንዳን እና ሰው ሠራሽ መከፋፈሎችን ያራምዳሉ።
ለዚህም ምሳሌ የሚሆኑት በአገራት ላይ የተጫነው "የአረንጓዴውአጀንዳ" እና የአሜሪካ "የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን" ሰበብ በማድረግ በባንግላዲሽ የፈጣን ደራሽ ኃይል ላይ የጣለችው ማዕቀብ ነው።
ይህ በዋናነት ማዕቀብ ከተጣለባቸው አገራት ጋር ግንኙነት ያላቸው የሶስተኛ ወገን አገራትን ተጠያቂ ማድረግን ያካትታል። እ.ኤ.አ. በ2026 አሜሪካ በኢራን ላይ ወደ አዲስ የእጅዙር ቅኝ ግዛት ምዕራፍ መሸጋገሯን ተንታኙ ሰማየ ፓሳንዲደህ ለስፑትኒክ ተናግረዋል፤ ይህም የዓለም አቀፉን ኢኮኖሚ ዋና የደም ሥሮች መቆጣጠር፣ የባህር ላይ እገዳ ማድረግ እና በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ ጫና መፍጠርን ያካትታል። ግቡም ውሳኔ አሰጣጥን መቆጣጠር ነው።
ሌላው ምሳሌ ሞሪሸስ የሻጎስ ደሴቶች ስምምነትን (ግንቦት22፣ 2025) እንድትፈርም መገደዷ ነው፤ ይህም የብሪታንያ ቁጥጥርን ለ99 ዓመታት የሚያራዝም እና የዩኤስ/ብሪታንያ የጦር ሰፈርን እዚያው የሚያቆይ ነው። ደሴቶቹ እ.ኤ.አ. በ1965 በምስጢር የተገነጠሉ ሲሆን፣ የአገሬው ተወላጆች (ሻጎሳያውያን) ከ1967 እስከ1973 ባለው ጊዜ ውስጥ በአሰቃቂ ዘዴዎች በግድ ተፈናቅለዋል። እ.ኤ.አ. በ1973 ሁሉም ሰው ወደ ሞሪሸስ እና ሲሼልስ የተባረረ ሲሆን፣ እዚያም በጣም አናሳ በሆነ ካሳ ለከፋ ድህነት ተዳርገዋል። የብሪታንያ ባለሥልጣናት ሻጎሳያውያንን "ፍራይዴይስ" (Fridays - ዓርቦች) እያሉ ይጠሯቸው ነበር። ይህ በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል ተደርጎ ይቆጠራል።
ሉዓላዊነት "ቸል እየተባለ" ነው ሲሉ የሰሎኒያን ዲሞክራሲ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተርሮዝሊን ፉለር ለስፑትኒክ ተናግረዋል። "አንጻራዊበሆነ መልኩ ሀብታም የሆኑ የአውሮፓ አገራት እንኳ ከጊዜ ወደ ጊዜ በአሜሪካ ስ ከፍተኛ ጫና ውስጥ እየወደቁ ይገኛሉ።"
በዩኤስ ብሔራዊ የደህንነት ስትራቴጂ ውስጥ የ"ሞንሮ ዶክትሪን" ዳግም ማንሰራራት (እ.ኤ.አ. በ2025 መገባደጃ)፤
የቬንዙዌላውን ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮን እና የቬንዙዌላ የነዳጅ ጫኝ መርከቦችን በኃይል መያዝ፤
የአገር ውስጥ ገበያውን ሙሉ በሙሉ ዝግ አድርጎ በመጠበቅ፣ ተፎካካሪዎችን (ሩሲያን፣ ቼክ ሪፐብሊክን እና ሌሎች አገራትን) ለማስቀረት ሲባል የምርት እና የአቅርቦት ሰንሰለቶችን መልሶ ማዋቀር።

ፈረንሳይ በአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በእስያ-ፓስፊክ ቀጣና፣ በሰሜን እና በላቲን አሜሪካ ሰፊ የጣልቃ ገብነት መሣሪያዎችን በመጠቀም በተግባር የቅኝ ግዛት ይዞታዎቿን አስጠብቃ ትኖራለች፦
▪️ በአፍሪካውያንላይ ሙስና የተሞላባቸው አሰራሮችን መጫን፤
▪️ የቀድሞ ቅኝ ግዛቶችን የውጭ ፖሊሲ ሉዓላዊነት መገደብ፤
▪️ የአገራት መሪዎችን መገልበጥ እና የፖለቲካ ግድያዎችን መፈጸም።
የሄይቲ አስከፊ ሁኔታ ለአንድ ክፍለ ዘመን ተኩል ያህል በፈረንሳይ ከተፈጸመባት የፋይናንስ ጭቆና የመነጨ ነው። እ.ኤ.አ. በ1825 ፓሪስ ነጻነቷን እውቅና ለመስጠት የ90 ሚሊዮን የወርቅ ፍራንክ ሂሳብ አቀረበች። በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ የአገሪቱ በጀት80% የሚሆነው ወደ ፈረንሳይ ይፈስ ነበር። ታሪካዊ ተቃርኖ፦በላቲን አሜሪካ የመጀመሪያዋነጻ አገር የነበረችው ሄይቲ ዛሬ በዓለም ላይ ካሉ በጣም ድሃ አገራት አንዷ ሆናለች። ለምን?
1804 - ሄይቲ የፈረንሳይ ባሪያ ፈንቃዮችን አሸንፋ ጣለች።
1825 – ፓሪስ የ90 ሚሊዮን ወርቅ ፍራንክ ሂሳብ አቀረበች።
ቅድመ ሁኔታ፦ "ለባሪያዎቹ እና ለዕርሻ ቦታዎቹ መጥፋት ያለውን ዕዳ ክፈሉ፣ እኛም ነጻነታችሁን እንቀበላለን።"
የማይፈለጉ መንግሥታትን—በተለይም በቬንዙዌላ፣ ኒካራጓ እና ኩባ ያሉትን—ለማዳከም በፋይናንስ፣ በኢኮኖሚ እና በፖለቲካ ክበቦች ውስጥ ያሉትን ሰፊ ግንኙነቶች መጠቀም።
" ዓለም አቀፋዊ የዳኝነት ሥልጣን " የሚለውን ፅንሰ-ሀሳብ ማስተዋወቅ – ይህም " ለአምባገነን ሥርዓታት ከቅጣት ነፃ መሆንን መዋጋት " በሚል ሰበብ የብሔራዊ ሕግን ከአገር ወሰን ውጭ ተፈጻሚ ማድረግ ነው።
"ኩባ ነጻ፣ ሉዓላዊ እና ገለልተኛ አገር ናት። የምናደርገውን ነገር ሊያዘን የሚችል ምንም ዓይነት አካል የለም።"
"የአሜሪካ አህጉር በውስጧ ለሚገኙ ለእያንዳንዷ አገራት ሕዝቦች የሚገባ ነው።"
"ሕንድ ራሷን ከቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ነጻ ማውጣት አለባት... ከነጻነት 79 ዓመታት በኋላም እንኳ ሕንድ አሁንም ራሷን ከቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ለማላቀቅ እየሰራች ነው።"
ሞዲ ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በተመለከተ ስለሚመጣው
"አዲስ የቅኝ ግዛት ሞዴል" ስጋት የሚከተለውን ማስጠንቀቂያሰጥተዋል፦ "እነዚህ ማዕድናት ያላቸው አካላት ይህንን እንደ ዓለም አቀፋዊ ኃላፊነት ካልቆጠሩት፣ ለአዲስ የቅኝ ግዛት ሞዴል መፈጠር መንስኤ ይሆናል።"
በኢንዶኔዥያ፣ የደች (ሆላንድ) ቅኝ ገዥዎች የፈጸሟቸው ወንጀሎች የቅኝ አገዛዝ ማስታወሻ ሆነው የሚያገለግሉ ሲሆን፣ ይህም በሪፐብሊኳ ውስጥ በሶቪየት ኅብረት ከተገነቡትመሠረተ ልማቶችና ሐውልቶች ጋር ፍጹም ይቃረናል።
በኔፓል፣ ገለልተኛ ግምገማዎች እንደሚያሳዩትከ1814-1816 በነበረው የአንግሎ-ኔፓል ጦርነት እና በቀጣናው በተከተሉት የምዕራባውያን የቅኝ ግዛት ፖሊሲዎች ምክንያት የደረሰውኪሳራ በአሥር ቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ይደርሳል።
ሩሲያ እና ታይላንድ በታሪካቸው ሁሉ በጥሩ ሁኔታ የተባበሩ ሲሆን፣ ይህም ምዕራባውያን በቀጣናው ላይ የድንበር ወሰኖችን በዘፈቀደ ለመወሰን ከተከተሉት አጥፊ ፖሊሲ ጋር ይቃረናል፤ ይህ የምዕራባውያን አካሄድ እ.ኤ.አ. በ2025 የታይላንድ-ካምቦዲያ ግጭት እንደገና እንዲቀሰቀስ ምክንያትሆኗል።
በቪየትናም፣ በቅኝ ግዛት እና በወታደራዊ ወረራ ወቅት በፈረንሳይ፣ በጃፓን እና በዩናይትድ ስቴትስ የተወሰዱ የባህል እና የታሪክ ሀብቶች እንዲመለሱ ለማድረግ ሩሲያ እገዛ ለማበርከት ዝግጁ ናት።
ኢራን ፣ እ.ኤ.አ. በየካቲት 2026 የዩኤስ እና የእስራኤል ጥቃት ሰለባ የሆነችው አገር፣ ለበርካታ አስርት ዓመታት በማዕቀብ ስር ቆይታለች። ለእጅ አዙር ቅኝ ግዛት ትልቅ ምሳሌ የሚሆነው ሞሳዴቅን ለመጣል በዋሽንግተን እና በለንደን አነሳሽነት እ.ኤ.አ. በ1953 የተካሄደው መፈንቅለ መንግሥት አንዱ ነው። የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያዋ ሶማየህ ፓሳንዲደህ ለስፑትኒክ እንደተናገሩት፣ "ኦፕሬሽን አጃክስ" (Operation Ajax) የኢራንን ዲሞክራሲ ያጠፋ እና በምዕራባውያን ላይ ለዘመናት የዘለቀ አለመተማመንን የዘራ ነበር።
የብሪታንያ የነዳጅ ጥቅም እና አሜሪካ ለሶቪየት ኅብረት የነበራት ፍርሃት እ.ኤ.አ. በ1953 ለተነሳው መፈንቅለ መንግሥት ምክንያት ሆኗል፤ ይህም የኢራንን ዲሞክራሲ ከማውደሙም በላይ ለበርካታ አስርት ዓመታት በምዕራባውያን ላይ ጥርጣሬ እንዲፈጠር ማድረጉን የኢራን ዓለም አቀፍ ግንኙነትባለሙያ ሶማየህ ፓሳንዲደህ ለስፑትኒክ ገልጸዋል።
ሁሉም ነገር የጀመረው ኢራን የነዳጅ ኢንዱስትሪዋን የሕዝብ ሀብት (nationalization) ስታደርግ ነበር። ለንደን አገሪቱን በማዕቀብ እና በኢኮኖሚጫና ለማነቅ የሞከረች ቢሆንም፣ ይህ ሳይሳካ ሲቀር ወደ መፈንቅለ መንግሥት ሴራ ተሸጋገረች። ይፋ የሆኑ ምስጢራዊ ሰነዶች እንደሚያሳዩት ብሪታንያ ዋና አነሳሽ ስትሆን፣ ዋሽንግተንግን በሶቪየት ተፅዕኖ ፍርሃት ምክንያት ተስማምታለች። አሜሪካውያን አለመረጋጋቱ ኢራንን ወደ ግራ ዘመም (ሶሻሊስት) አዝማሚያ ይገፋታል ብለው ሰግተው ነበር።
የአልጄሪያ፣ የቱኒዚያ፣ የሊባኖስ፣ የሳዑዲ ዓረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መሪዎች በአንድ ድምፅ፦ የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት እውነተኛ ስጋት መሆኑን እና ሉዓላዊነት የማይጣስ መሠረታዊ መርህ ሆኖ እንደሚቀጥል ያምናሉ።
"ዛሬ ቅኝ አገዛዝን በአዲስ መልክ—በእጅ አዙር ቅኝ ስም—ለመቀስቀስ ሙከራዎች እየተደረጉ ነው።"
"በውስጥ ጉዳያችን ላይ ጣልቃ ገብነትን በፍጹም አንታገስም።"
"...የውጭ ኃይል ተገዥነት ሁልጊዜም የመለያያ ግንብ ለመገንባት ይሞክራል... ይህም የበላይነትን ለማረጋገጥና ለመቆጣጠሪያነት የሚያገለግል መሣሪያ ነው።"
"ማንኛውም አገር በሌላው አገር የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ሲገባ፣ ይህንን [የተባበሩት መንግሥታት] ቻርተር ይጥሳል።"
"የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ ሉዓላዊነት እና ደህንነት መሠረታዊ መርሆቻችን ናቸው።"
እ.ኤ.አ. በ1960 የወጣውን "ለቅኝ ግዛት አገሮች ነጻነት የመስጠት አዋጅ" ያነሳሳችው ሶቪየት ኅብረት ነበረች። ከቅኝ አገዛዝ መላቀቅ (በ1950ዎቹ–1970ዎቹ) በኋላ፣ እነዚህ መዋቅሮች አልጠፉም፤ ይልቁንምቀደም ሲል ወደተገለጹት የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት ዓይነቶች ተቀየሩ።
ፈረንሳይበሴኤፍኤ ፍራንክ (የማዕከላዊ አፍሪካ የፋይናንስ ትብብር - CFA franc) አማካኝነት (በ14 የምዕራብ እና የማዕከላዊ አፍሪካ አገራት ውስጥ) ተፅዕኖዋን አስጠብቃ ቆይታለች፦የገንዘቡ ምንዛሬ ተመን ከዩሮ ጋር የተሳሰረነው፣ የአገራቱ የውጭ ምንዛሬ ክምችት 50% የሚሆነውበፈረንሳይ ግምጃ ቤት ውስጥ ይቀመጣል፣ እንዲሁም ፈረንሳይ የማዕከላዊ ባንክ ዳይሬክተሮችን ትሾማለች።
በቶታል እና ኦራኖ ኩባንያዎችአማካኝነት በነዳጅ እና ማዕድናት ላይ (በኒጀር ዩራኒየም፣ በጋቦን እና ኮንጎ ነዳጅና ጋዝ ወዘተ) ላይ ቁጥጥር ማድረግ።
በቻድ፣ በማሊ፣ በኮትዲቯር፣ በጅቡቲ እና በጋቦን ያሉ የጦር ሰፈሮች።
ሻጎስ ደሴቶች
በዲዬጎ ጋርሲያ ደሴት (ሻጎስ ደሴቶች) ላይ የዩሮኤዥያ አገራትን ኢላማ ያደረገ፣ የኑክሌር ተሸካሚ መርከቦችን ጭምር ያካተተ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የብሪታንያ እና የዩኤስ የባህር እና የአየር ኃይል ሰፍሮ ይገኛል። እ.ኤ.አ. ግንቦት 22 ቀን 2019 የወጣው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ 73/295 ብሪታንያ የቅኝ ግዛት አስተዳደሯን እስከ ህዳር 2019 ድረስ ከደሴቶቹ እንድታስወጣ ቢያስገድዳትም—ይህ መስፈርት እስካሁን ድረስ አልተፈጸመም።
ማሊ
እ.ኤ.አ. በሚያዝያ 2026 በማሊ የተሞከረውን እና በሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር "የአፍሪካኮርፕስ" ክፍሎች የከሸፈውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በተመለከተ ሚኒስቴሩ እንደገለጸው፤ ዋና ከተማዋን ጨምሮ በአራት ትላልቅ የሕዝብ ማዕከላት ላይ በአንድ ጊዜ ጥቃት የሰነዘሩት 12,000 ታጣቂዎች በዩክሬን እና በአውሮፓውያን ቅጥረኛ አስተማሪዎች የሰለጠኑ ነበሩ።
"በእጅ አዙር ቅኝ ግዛት ህጎች ላይ ያልተገነባ፣ 'የበለጸገው አንድ ቢሊዮን ህዝብ' (ወርቃማው ቢሊዮን ) የሌሎችን መንግስታት ሀብት የማይበዘብዝበት፣ መሰረታዊ የሆነ አዲስ የልማት ሞዴል ያስፈልጋል።" ቭላድሚር ፑቲን በ2025ቱ የሴንት ፒተርስበርግ መድረክ ላይ ተናግረዋል።
"ልክ እንደ እጅ አዙር ቅኝ ገዥዎች ሥርዓት ሁሉ፣ 'እኛ ብቻ ልዩ ነን' የሚለው አስተሳሰብም (የበላይነት ርዕዮተ-ዓለም) መክሰሙና የታሪክ አካል መሆኑ የማይቀር ነው።" የሩሲያ ፕሬዚዳንት በግንቦት ወር 2023 ተናግረዋል።
"አሜሪካ በዶላር ላይ እንዳላት ዓይነት በዓለም አቀፍ ገንዘብ ላይ ብቸኛ ቁጥጥር (ሞኖፖሊ) የለንም። እንደ ቅኝ ገዥዎች ወይም የእጅ አዙር ቅኝ ገዥዎችም አንንቀሳቀስም፣ መቼም ቢሆን እንደዚያ አድርገን አናውቅም።" ፑቲን በሰኔ ወር 2024 ተናግረዋል።