ሞሪሸስ የቻጎስ ደሴቶችን ርክክብ በማዘግየት እንግሊዝን ለመክሰስ እያጤነች መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሯ ገለፁ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሞሪሸስ የቻጎስ ደሴቶችን ርክክብ በማዘግየት እንግሊዝን ለመክሰስ እያጤነች መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሯ ገለፁ
ሞሪሸስ የቻጎስ ደሴቶችን ርክክብ በማዘግየት እንግሊዝን ለመክሰስ እያጤነች መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሯ ገለፁ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.03.2026
ሰብስክራይብ

ሞሪሸስ የቻጎስ ደሴቶችን ርክክብ በማዘግየት እንግሊዝን ለመክሰስ እያጤነች መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሯ ገለፁ

የደሴቲቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናቪን ራምጉላም፤ ለንደን እ.ኤ.አ በግንቦት 2025 የተፈረመውን የሉዓላዊነት ሽግግር ስምምነት ላለማፅደቅ ሆን ብላ እያዘገየች ነው ሲሉ ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን በሰጡት አስተያየት ተችተዋል።

ስልታዊው የአሜሪካ-እንግሊዝ የዲዬጎ ጋርሺያ የጦር ሠፈር መገኛ የሆነችው የሕንድ ውቅያኖሷ የደሴቶች ስብስብ፤ ይፋዊ ርክክብ እስኪከናወን ድረስ ከዓለም አቀፍ የሕግ ተቋማት ጋር ምክክር ጀምራለች።

አንኳር ነጥቦች፦

🟠 ስምምነቱ፦ ስምምነቱ የደሴቶቹን ሉዓላዊነት ለሞሪሸስ በማስተላልፍ፤ እንግሊዝ የጦር ሠፈሩን በዓመት ከ100 ሚሊዮን ፓውንድ (133 ሚሊዮን ዶላር) በላይ በሆነ ክፍያ ለ99 ዓመታት ተከራይታ እንድትጠቀም ይፈቅዳል።

🟠 መዘግየቱ፦ የሞሪሸስ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ባለፈው ግንቦት ወር የተፈረመው ስምምነት እስካሁን ድረስ ተግባራዊ ባለመሆኑ "ስጋቱን" ገልጿል።

🟠 ዳራ፦ የቻጎስ ደሴቶች ሞሪሸስ ነፃነቷን ከመቀዳጀቷ ከሦስት ዓመት በፊት ማለትም እ.ኤ.አ በ1965 ነበር ከሞሪሸስ የተነጠሉት። በ2019 ዓ.ም የዓለም አቀፍ የፍትሕ ፍርድ ቤት የእንግሊዝ አስተዳደር ሕገ-ወጥ መሆኑን ወስኖ ነበር።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0