በእንግሊዝ ጦር የመቅደላ ዘመቻ በኃይል የተዘረፈን ዕቃ መሸጥ ተቀባይነት የለውም - አሉላ ፓንክረስት

ሰብስክራይብ

በእንግሊዝ ጦር የመቅደላ ዘመቻ በኃይል የተዘረፈን ዕቃ መሸጥ ተቀባይነት የለውም - አሉላ ፓንክረስት

በመቅደላ ጦርነት ወቅት ከኢትዮጵያ የተዘረፈ የብራና መጽሐፍ ቅዱስ በአቡ ዳቢ በ250,000 ዩሮ ለሽያጭ መቅረቡን አስመልክቶ ከስፑትኒክ አፍሪካ ተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ማኀበር የቦርድ አባል ዶ/ር አሉላ ፓንክረስት፤ መጽሐፉ የኢትዮጵያ ባሕላዊ ቅርስ ነው ብለዋል።

"የኢትዮጵያ ባሕላዊ ቅርስ በግል ስብስብ ውስጥ ሊቀመጥ አይገባም። ወደ ኢትዮጵያ መመለስ አለበት" ሲሉ አሳስበዋል።

እ.ኤ.አ ከ1730-1740 ጎንደር ውስጥ በብራና በግዕዝ ቋንቋ የተጻፈ ነው የሚባለው ይህ መጽሐፍ፤ ሙሉውን የሉቃስ ወንጌል እና የዮሐንስ ወንጌልን እስከ መጨረሻዎቹ 16 ቁጥሮች ድረስ ይዟል።

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0