- Sputnik አፍሪካ, 1920
Turning Africa Forward
በአህጉሪቱ ስልታዊ መነቃቃት ላይ ግልጽ እይታን የሚሰጥ በስፑትኒክ አፍሪካ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ፕሮግራም ። ከዜናዎች ባሻገር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን እየተለወጠ የመጣ ሚና በጥልቀት ይተነትናል፤ የወደፊቱን የዓለም ሥርዓት በመቅረጽ ረገድ ያለውን አቅጣጫ በሰፊው ይዳስሳል።

የአፍሪካ የተዘረፉ ቅርሶችን የማስመለስ ዓለም አቀፍ ትግል

የአፍሪካ የተዘረፉ ቅርሶችን የማስመለስ ዓለም አቀፍ ትግል
ሰብስክራይብ
''በጦርነትና በወረራ ከተዘረፉ ቅርሶች በንግድ መልክ ገንዘብ ለመስበስብ የሚደረግ ጥረት በምንም መስፈርት ተቀባይነት የሌለው የሞራል ውድቀት ነው። ቅርሶቻችንን በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከፍለን የምንገዛበት ሳይሆን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበት አዲስ የትግል ምዕራፍ ላይ እንገኛለን፤'' ሲሉ የታሪክ ተመራማሪና አንትሮፖሎጂስቱ አሉላ ፓንክኸርስት(ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።
​በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፖድካስት ክፍላችን፤ ሞስኮ ለአፍሪካ ታሪካዊ ፍትህና የቅርሶች መመለስ ያሳየችውን ድጋፍ፣ 500,000 የሚሆኑ የአፍሪካ የጥበብ ሀብቶች በውጭ ሀገራት መበተናቸውን፣ እና በ1868 በመቅደላ ከተዘረፉት መካከል በቅርቡ በ250,000 ዩሮ አቡዳቢ ውስጥ ለጨረታ የቀረበውን የ18ኛው ክፍለ ዘመን የጎንደር ወንጌል ያለ ክፍያ ወደ ሀገሩ እንዲመለስ የሚደረገውን ዓለም አቀፍ የህግና የዲፕሎማሲ ትግል ከአሉላ ፓንክኸርስት(ዶ/ር) ጋር ያደረግነውን ውይይት ይዘንላችሁ ቀርበናል።
​ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ሙሉ ፕሮግራሙን ይከታተሉ ፡

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ፡ ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0