- Sputnik አፍሪካ, 1920
Turning Africa Forward
በአህጉሪቱ ስልታዊ መነቃቃት ላይ ግልጽ እይታን የሚሰጥ በስፑትኒክ አፍሪካ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ፕሮግራም ። ከዜናዎች ባሻገር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን እየተለወጠ የመጣ ሚና በጥልቀት ይተነትናል፤ የወደፊቱን የዓለም ሥርዓት በመቅረጽ ረገድ ያለውን አቅጣጫ በሰፊው ይዳስሳል።

18ኛው የብሪክስ ጉባኤ፡ የፋይናንስ ሉዓላዊነት እና የደቡብ ዓለም አዲስ የፖለቲካ-ምጣኔሀብት ምዕራፍ

18ኛው የብሪክስ ጉባኤ፡ የፋይናንስ ሉዓላዊነት እና የደቡብ ዓለም አዲስ የፖለቲካ-ምጣኔሀብት ምዕራፍ
ሰብስክራይብ

''በኒው ዴልሂ በተካሄደው 18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ የተስተዋለው ዋናው ነገር ብሪክስ ከተራ ውይይት አልፎ ወደ ተግባራዊ ተቋማዊ አደረጃጀት እና ለውጥ እየተሸጋገረ መሆኑን ነው። በተለይም የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት ጥረት፣ የዓለም አቀፍ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ምክር ቤት ዕጩነት፣ የኮፕ32 አዘጋጅነት፣ እንዲሁም በቀይ ባሕር አካባቢ ፍትሐዊ የባሕር በር ማግኘት እና የአፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ማግኘትን አስመልክቶ የጋራ አቋም የተያዘበት ታሪካዊ መድረክ ነው፤'' ሲሉ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ጥናትና ምርምር ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጋሻው አይፈራም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፕሮግራማችን፤ በኒው ዴልሂ የተካሄደውን የ18ኛውን የብሪክስ ጉባኤ ዋና ዋና ውሳኔዎች፣ የኢትዮጵያን የንግድ እና የዲፕሎማሲ ስኬቶች፣ የዶላር የበላይነትን ለመቀነስ የቀረቡ የሀገር ውስጥ ገንዘብ የንግድ ልውውጥ እና የድንበር ተሻጋሪ የክፍያ ሥርዓቶችን፣ ኢትዮጵያ የአዲሱ ልማት ባንክ የክልላዊ ቢሮ በአዲስ አበባ እንዲከፈት ያቀረበችውን ጥሪ፣ እንዲሁም የቀይ ባሕር እና የሱዳን ሰላም ጉዳዮችን በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ጥናትና ምርምር ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጋሻው አይፈራም ጋር በጥልቀት ተወያይተናል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ይከታተሉ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0