- Sputnik አፍሪካ, 1920
Turning Africa Forward
በአህጉሪቱ ስልታዊ መነቃቃት ላይ ግልጽ እይታን የሚሰጥ በስፑትኒክ አፍሪካ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ፕሮግራም ። ከዜናዎች ባሻገር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን እየተለወጠ የመጣ ሚና በጥልቀት ይተነትናል፤ የወደፊቱን የዓለም ሥርዓት በመቅረጽ ረገድ ያለውን አቅጣጫ በሰፊው ይዳስሳል።

የአፍሪካ ቋንቋዎችና 'ኤአይ'፦ ከምዕራባውያን የበላይነት ወደ ዲጂታል ሉአላዊነት

የአፍሪካ ቋንቋዎችና 'ኤአይ'፦ ከምዕራባውያን የበላይነት ወደ ዲጂታል ሉአላዊነት
ሰብስክራይብ

''የአፍሪካ ቋንቋዎችን በዲጂታል አካታች ማድረግ የሚቻለው የምዕራባውያንን የቋንቋ ሞዴሎች በአፍሪካ እውነታዎች ላይ በግድ በመጫን አይደለም፤ የዲጂታል ስርዓቶች የጾታ አገላለጽን ሲያዛቡ ወይም አካባቢያዊ የአነጋገር ዘይቤዎችን ሲስቱ፣ ይህ ተነጥሎ የሚታይ የቴክኒክ ችግር ሳይሆን የአፍሪካን ሰዋሰዋዊ መዋቅሮች በዝምታ የሚያጠፉ፣ የአፍሪካን እውነታ የማያንጸባርቁና በምዕራባውያን ማዕከልነት የተቃኙ የመረጃ ቋቶች ውጤት ነው'' ሲሉ በምስራቅ አፍሪካ የሂሳብ ሳይንስ ምርምርና ኢኖቬሽን ማዕከል የኤአይ እና ኤንኤልፒ ተመራማሪው ዋለልኝ ተዋበ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት፤ በመጀመሪያው ክፍል ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የቋንቋ ማቀናበሪያ ቴክኖሎጂዎች ከአፍሪካ ቋንቋዎች ህልውና ጋር ያላቸውን ቁርኝት፣ ከሰው ሰራሽ አስተውሎትና ተፈጥሯዊ የቋንቋ ፕሮሰሲንግ ተመራማሪው ዋለልኝ ተዋበ (ዶ/ር) ጋር በጥልቀት እንወያያለን። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ፤ ወደ አለም አቀፉ የኤአይ ሉዓላዊነትና የብዙ-ዋልታ ስርዓት በመሸጋገር፤ በሻንጋይ የተመሰረተው የአለም አቀፍ ኤአይ ትብብር ድርጅት ለአፍሪካና ለታዳጊ ሀገራት የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የውድድር አቅም እና የዲጂታል ሉዓላዊነት መከበር ያለውን ፋይዳ ከኤአይ አስተዳደርና እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂካዊ አማካሪው ቱሁ ኑግራሃ ጋር ሰፊ ውይይት አድርገናል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ይከታተሉ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0