- Sputnik አፍሪካ, 1920
Turning Africa Forward
በአህጉሪቱ ስልታዊ መነቃቃት ላይ ግልጽ እይታን የሚሰጥ በስፑትኒክ አፍሪካ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ፕሮግራም ። ከዜናዎች ባሻገር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን እየተለወጠ የመጣ ሚና በጥልቀት ይተነትናል፤ የወደፊቱን የዓለም ሥርዓት በመቅረጽ ረገድ ያለውን አቅጣጫ በሰፊው ይዳስሳል።

አገራዊ ምክክር፦ያለውጭ ጣልቃገብነት ''ብሔራዊ መግባባትን የማረጋገጥ ጉዞ''

አገራዊ ምክክር፦ያለ ውጭ ጣልቃገብነት '' ብሔራዊ መግባባትን የማረጋገጥ ጉዞ''
ሰብስክራይብ

''ታሪካዊው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ጉባኤ፤ ለሀገራዊ ችግሮች ከምዕራባውያኑ የሚመጣን አንድን መፍትሄ ለሁሉም የሚል አንድ መጠን ለሁሉም ይበቃል ‘one-size-fits-all approach’ በመተው፣ አገሪቱ ብቻ ሳትሆን መላው አፍሪካ እና የደቡቡ ንፍቀ ክበብ ያለ ውጭ ጣልቃገብነት የራሳቸውን ሰላም በራሳቸው እውቀትና ፍልስፍና መገንባት እንደሚችሉ በተግባር የሚያሳይ ታላቅ ማረጋገጫ ነው'' ሲሉ የፖሊሲ እና አስተዳደር ምሁሩ ጂሬኛ ታደሰ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት የመጀመሪያው ክፍል ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የጀመረውን የኢትዮጵያ ታሪካዊ የምክክር መድረክ መነሻ አድርገን አፍሪካ ለችግሮቿ መሰል የምክክር መንገዶች ያላቸውን አቅም እንፈትሻለን፡፡ ለዚህም የፖሊሲ እና አስተዳደር ምሁሩ ጂሬኛ ታደሰን ጋብዘናቸዋል። በሁለተኛው ክፍል ሰው ሰራሽ አስተውሎት በኪነጥበብ ዘርፍ ለአፍሪካ የፈጠራ ባለሙያዎች እንዴት ረዳት ሊሆን ይችላል ስንል ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ በተፈጥሮ የቋንቋ 'ፕሮሰሲንግ' ፣ ማሽን ለርነንግ' እና ዳታ ሳይንስ ተመራማሪ ወንድወሰን ሙሉጌታ (ዶ/ር)ን አነጋግረናል። በመጨረሻም የአካባቢ ጥበቃ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ መረጃ-ተኮር እና በይነ-መረባዊ የካርታ ስራዎችን በመጠቀም የተፈጥሮ ሀብቶችን እና የዱር እንስሳቶችን ከጥፋት ለመታደግ የሚደረጉ ጥረቶችን በተመለከተ የብዝሃሕይወት እና የዱር እንስሳት ጥበቃ ተመራማሪ ዘላለም ተፈራ (ዶ/ር) በስፋት ተመልክተነዋል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ይከታተሉ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0