አዲሱ የተሽከርካሪዎች ሰሌዳ አጠቃላይ መረጃዎችን የያዘ ቺፕስ በውስጡ መቀበሩ ተገለፀ

ሰብስክራይብ

አዲሱ የተሽከርካሪዎች ሰሌዳ አጠቃላይ መረጃዎችን የያዘ ቺፕስ በውስጡ መቀበሩ ተገለፀ

"ሰሌዳው በውስጡ ቻንሲ፣ ሞተር፣ የባለቤቱን ስም እና ሌሎች መረጃዎችን የያዘ ቺፕስ በውስጡ ተቀብሯል፡፡ ይህም አገራዊ የተሽከርካሪዎች የመረጃ ቋት ለመፍጠር ያግዛል" ሲሉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ፈቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን የቂርቆስ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ደረጄ አሰፋ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በክፍለ ከተማው ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ አገልግሎቱ መስጠት መጀመሩን የተናገሩት ሥራ አስኪያጁ፣ አዲሱ ሰሌዳ የአገር ሃብትን ከብክነት ለመታደግ እና ሕገ-ወጥነትን ለመከላከል የላቀ እገዛ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0