የአፍሪካ በምዕራባውያን ዕርዳታ ላይ ጥገኛ መሆን ለአሜሪካ እና ለአውሮፓ ሕብረት አጀንዳዎች እንድትገዛ ያስገድዳታል - ኬንያዊ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

የአፍሪካ በምዕራባውያን ዕርዳታ ላይ ጥገኛ መሆን ለአሜሪካ እና ለአውሮፓ ሕብረት አጀንዳዎች እንድትገዛ ያስገድዳታል - ኬንያዊ ባለሙያ

የፖለቲካ ተንታኙ አሌክስ ዋንዛላ ለስፑትኒክ አፍሪካ ሲናገሩ፤ አሜሪካ እና የአውሮፓ አገራት ለአፍሪካ አገራት ሰብዓዊ፣ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ድጋፎችን በሚያደርጉበት ወቅት የሚመሩት በራሳቸው ፍላጎት ነው ብለዋል።

እነዚህ ለጋሾች የተወሰኑ የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን ለመጠየቅ ይህንን ተፅዕኖ በተደጋጋሚ ጊዜ እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙበት ሲሆን፣ ሌላው ቀርቶ በምርጫ ውጤቶች ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር ጭምር ሊሞክሩ እንደሚችሉ ባለሥልጣኑ ጠቁመዋል።

በዚህም ምክንያት፤ በውጭ ዕርዳታ ላይ ከመጠን በላይ ጥገኝነት ያላቸው አገራት ራሳቸውን ችለው ገለልተኛ ውሳኔዎችን የማሳለፍ አቅማቸውን የማጣት አደጋ ይጋረጥባቸዋል ሲሉ ተናጋሪው አፅንዖት ሰጥተው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0