የቻይንኛ ቋንቋን በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ለማካተት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ
16:19 11.06.2026 (የተሻሻለ: 16:24 11.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የቻይንኛ ቋንቋን በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ለማካተት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ
ለአምስት ዓመታት የሚቆየውን የሁለትዮሽ ስምምነት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በይፋ ተፈራርመዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው፣ ይህ ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት፣ ቱሪዝምና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ከማሳደግ ባለፈ፣ ቻይና ለኢትዮጵያውያን በምታመቻቸው የትምህርት ዕድሎች አማካኝነት ሀገሪቱ በላቀችበት የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዙሪያ የዕውቀት ልውውጥ ለማድረግ ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል ሲሉ ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሄ በበኩላቸው፣ በአሁኑ ወቅት በቻይና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የአማርኛ ቋንቋን ማስተማር መጀመሩ የሀገራቱን ታሪካዊ ግንኙነት ይበልጥ ያጠናከረና አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን አስታውቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X