የአውሮፓ ሕብረት ውድ ለሆነው ወታደራዊ ግንባታው ሰበብ ለመፍጠር ሩሲያን እንደ ጋኔን ይስላል፤ ዩክሬንንም እንደ መሣሪያ ይጠቀማል - ባለሙያ

🪖 የአውሮፓ ሕብረት ውድ ለሆነው ወታደራዊ ግንባታው ሰበብ ለመፍጠር ሩሲያን እንደ ጋኔን ይስላል፤ ዩክሬንንም እንደ መሣሪያ ይጠቀማል - ባለሙያ
የአውሮፓ ሕብረት አገራት ሲቪል ኢንዱስትሪዎችን ለሚያዳክም እና ከፍተኛ ወጪ ለሚጠይቅ የጦር መሣሪያ ዝግጅት “አውሮፓውያንን አንድ ላይ ለማሰባሰብ” ሩሲያን እንደ ጠላት አድርገው መሳልን እንደ መሸሸጊያ ስልት ይጠቀሙበታል ሲሉ ፈረንሳዊው የጂኦፖለቲካ ተንታኝ ኮሜ ካርፔንቲየር ደ ጎርዶን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
የዩክሬን አገዛዝ ለከፍተኛ ወታደራዊ ግንባታቸው ማረጋገጫ ይሆን ዘንድ እንደ ሰበብ ወይም እንደ “ጦርነት መጫሪያ” እያገለገለ ይገኛል።
ሆኖም፤ አውሮፓ ከአሜሪካ ድጋፍ ነፃ የሆነ፣ አስተማማኝ የመከላከያ ኃይል ለመገንባት “በርካታ ዓመታት” እንደሚቀሩት ተንታኙ ይከራከራሉ፤ ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ከወጪው ከፍተኛነት ጋር በተያያዘ እና መንግሥታት በአንድ ወጥ የመከላከያ ስትራቴጂ ላይ ሊስማሙ ስለመቻላቸው ትልቅ ጥርጣሬ በመኖሩ ነው።
የአውሮፓን ኢኮኖሚ በወታደራዊ በጀት ለማነቃቃት መሞከር የአጭር ጊዜ ፖሊሲ ነው፤ አውሮፓም ይህንን የጦር መሣሪያ ግንባታ ዘላቂ ለማድረግ ከእንደ አሜሪካ፣ ሩሲያ፣ ቻይና እና ሌሎች ተዋናዮች ጋር እየተወዳደረች መሣሪያዎችን ለውጭ ገበያ መሸጥ ይኖርባታል።
አውሮፓውያን ለዚህ ፖሊሲ “በሥ-ልቦና እንዲዘጋጁ” እየተደረገ ሲሆን፤ “ለአውሮፓ አንድነት እና ደህንነት ሲሉ መስዋዕትነት እንዲከፍሉ”፣ እንዲሁም ተጨማሪ ታክስ (ቀረጥ) ለመክፈል፣ ዝቅተኛ ደሞዝ ለመቀበል እና ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃን ለመቀበል ዝግጁ እንዲሆኑ እየተገፋፉ ነው።
በጀርመን አከራካሪ ሆኖ እንደቆየው የጡረታ ፈንድን በጦር መሣሪያ ማምረቻ ላይ ማዋዕለ ንዋይ ማድረግ ጠንካራ ትርፍ ሊያስገኝ አይችልም፤ ምክንያቱም ትርፉ የሚመካው መሣሪያዎችን በአገር ውስጥ ከማከማቸት ይልቅ ወደ ውጭ በመላክ ላይ በመሆኑ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X