ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች የመንግሥት የ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ልማት ፕሮግራም ማዕከል እንደሚሆኑ ተገለጸ

ሰብስክራይብ

ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች የመንግሥት የ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ልማት ፕሮግራም ማዕከል እንደሚሆኑ ተገለጸ

በአሁኑ ወቅት አንድ ቤት በአማካይ በዝቅተኛ ዋጋ 2 ሚሊዮን ብር ቢሰላ፤ ለ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ ወደ 3 ትሪሊዮን የኢትዮጵያ ብር እንደሚያስፈልግ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ሄለን ደበበ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ገልጸዋል።

አክለውም “የመሬት ዝግጅትን ጨምሮ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮችን ሚና፣ ግንባታውን በፍጥነት፣ በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ አቅርቦቶችን በጥናት የመለየት ሥራ እየተሠራ ነው” ብለዋል።

የጥናት ዶክመንቶቹ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ የሚገኙ በመሆኑ ፕሮግራሙ በቅርቡ በይፋ ተጀምሮ ዜጎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ጠቁመዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0