ኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ከአልጄሪያ የነዳጅ ዘርፍ ልምድ በመቅሰም እቅሟን የማሳደግ ዓላማ ያነገበ ስምምነት ላይ ደረሠች - ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

ኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ከአልጄሪያ የነዳጅ ዘርፍ ልምድ በመቅሰም እቅሟን የማሳደግ ዓላማ ያነገበ ስምምነት ላይ ደረሠች - ሚኒስትር

ኮንጎ እና አልጄሪያ በሃይድሮካርቦን (የነዳጅና ጋዝ) ዘርፍ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት በአልጀርስ መፈራረማቸውን የኮንጎ የሃይድሮካርቦን ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

በባሕር ዳርቻና በማዕከላዊ ተፋሰሶች ከፍተኛ የነዳጅና ጋዝ ሀብት ያላት ኮንጎ፤ ከአልጄሪያ ጋር የምታደርገውን የትብብር አቅጣጫ በአራት ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ከፍላለች፦

በነዳጅ ክምችት ይዞታዎች ላይ ኢንቨስትመንትን መሳብ፣

የነዳጅ መረጃ ሥርዓቶችን ማዘመን፣

የላይኛው ተፋሰስ አስተዳደርን ማሻሻል፣

በቴክኒክ መስኮች የጋራ ሥልጠናዎች።

በተጨማሪም ውይይቱ በነዳጅ ማጣራት፣ በማከማቸት፣ በፈሳሽ ጋዝ አስተዳደር እና በሎጅስቲክስ መሠረተ ልማት ዙሪያ ያሉ ጉዳዮችን ያካተተ እንደነበር መግለጫው አመልክቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0