ጊኒ ከ2021 የመፈንቅለ መንግሥት በኋላ የመጀመሪያውን የፓርላማ እና አካባቢያዊ ምርጫ እያካሄደች ነው - መገናኛ ብዙኃን
19:19 31.05.2026 (የተሻሻለ: 19:24 31.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ጊኒ ከ2021 የመፈንቅለ መንግሥት በኋላ የመጀመሪያውን የፓርላማ እና አካባቢያዊ ምርጫ እያካሄደች ነው - መገናኛ ብዙኃን
ከ6.8 ሚሊዮን በላይ የተመዘገቡ መራጮች በመላው ሀገሪቱ ሰላማዊ በሆነ መንፈስ፤ በግምት በ24,000 የምርጫ ጣቢያዎች ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛል። የአፍሪካ ኅብረት፣ የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ማኅበረሰብ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ታዛቢዎችም ሂደቱን እየተከታተሉ ነው።
ምርጫው ጊኒ ከወታደራዊ አገዛዝ ወደ ሕገ-መንግሥታዊ የሲቪል አስተዳደር የምታደርገው ሽግግር ሙሉ በሙሉ ማብቃቱን ያመለክታል ተብሎ ይጠበቃል። መራጮች 147 የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት እና የአካባቢ ምክር ቤት ተወካዮችን ለመምረጥ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ 350 ማዘጋጃ ቤቶች ድምጻቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።
ከመፈንቅለ መንግሥቱ በኋላ በታኅሣሥ ወር 2025 በተካሄደው የመጀመሪያው የጊኒ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ማማዲ ዱምቡያ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X