የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ የጤና ሚኒስትሮች በኢቦላ ወረርሽኝ ዙሪያ አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሂዱ ነው
15:57 31.05.2026 (የተሻሻለ: 16:04 31.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ የጤና ሚኒስትሮች በኢቦላ ወረርሽኝ ዙሪያ አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሂዱ ነው
ከሰኞ እስከ ማክሰኞ በበይነመረብ አማካኝነት የሚካሄደው ይህ ስብሰባ፤ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በኡጋንዳ የተቀሰቀሰውንና አሁንም በቀጠለው የኢቦላ ወረርሽኝ ላይ ለመምከር እንዲሁም የቀጣናውን የጋራ የመከላከል አቅም ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ መሆኑን የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ስብሰባው የበሽታውን ስርጭት ለመግታት በቀጣናው ደረጃ እንዲወሰዱ በቀረቡ የድርጊት መርኃ-ግብሮች ላይ ይመክራል።
የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ ሴክሬተሪያት የአስቸኳይ ጊዜ ስብሰባዎችን ከማዘጋጀት ጀምሮ ለኢቦላ ክትባቶች እና ሕክምናዎች የሚሆኑ ደንቦችን እስከ ማዋሃድ ድረስ ያሉ የቀጣናዊ ቅንጅት ሥራዎችን እያጠናከረ እንደሚገኝም በመግለጫው ተጠቁሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X