የዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል ኤጀንሲ ተቆጣጣሪዎች ዩክሬን በዛፖሮዢያ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ በድሮን ያደረሰችውን ጥቃት እንዲጎበኙ ፈቃድ አገኙ

© telegram sputnik_ethiopiaየዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል ኤጀንሲ ተቆጣጣሪዎች ዩክሬን በዛፖሮዢያ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ በድሮን ያደረሰችውን ጥቃት እንዲጎበኙ ፈቃድ አገኙ
የዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል ኤጀንሲ ተቆጣጣሪዎች ዩክሬን በዛፖሮዢያ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ በድሮን ያደረሰችውን ጥቃት እንዲጎበኙ ፈቃድ አገኙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 31.05.2026
ሰብስክራይብ

የዓለም አቀፉ የኒውክሌር ኃይል ኤጀንሲ ተቆጣጣሪዎች ዩክሬን በዛፖሮዢያ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ በድሮን ያደረሰችውን ጥቃት እንዲጎበኙ ፈቃድ አገኙ

የጣቢያው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኢቭጌኒያ ያሺና ለስፑትኒክ በሰጡት አስተያየት፤ “የአይ.ኤ.ኢ.ኤ ሠራተኞች ስለ ድርጊቱ መረጃ ደርሷቸዋል። ደኅንነቱ አስተማማኝ መሆኑ ሲረጋገጥም ወዲያውኑ ወደ ቦታው እንዲገቡ ይደረጋል” ብለዋል።

ዩክሬን ቅዳሜ ከሰዓት የኃይል ማመንጫውን የቱርቢና ኮሪደር ክፍል 6 ኢላማ አድርጋ በድሮን የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ ፍንዳታ ተከስቷል። ሆኖም ጉዳት ወይም የከፋ ውድመት ባለመድረሱ የጣቢያው የሥራ እንቅስቃሴዎች ያለምንም መቆራረጥ የቀጠሉ ሲሆን የራዲየሽን መጠኑም መደበኛ ሁኔታ ላይ ጸንቷል።

ሆኖም ድሮኑ የሕንጻው ግድግዳ ላይ ቀዳዳ ፈጥሯል። ድሮኑ ያጠቃው የተርባይን ክፍል ደግሞ ከኒውክሌር ማብለያው ጥቂት ርቀት ላይ ብቻ የሚገኝ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0