ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በቴክኖሎጂ የታገዘ የፀጥታና ደህንነት የማስከበር ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ
12:41 31.05.2026 (የተሻሻለ: 12:53 31.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በቴክኖሎጂ የታገዘ የፀጥታና ደህንነት የማስከበር ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ
የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል በሀገር አቀፍ ደረጃ የተደረጉ የምርጫ ዝግጅቶችን የገመገመ ከፍተኛ ስብሰባ ካካሄደ በኋላ፤ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን ለማረጋገጥ ቁርጠኛ እንደሆነ አረጋግጧል።
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፤ "የምርጫውን ሒደት ለማስተጓጎል በተለያዩ አካላት የተደረጉ ሙከራዎች በመከላከያ ሠራዊቱና በሌሎች የፀጥታ አካላት የተቀናጀ እርምጃ ሙሉ በሙሉ እንዲከሽፉ ተደርገዋል" ሲሉ ተናግረዋል።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በበኩላቸው፤ ግብረ-ኃይሉ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር መረጃዎችን በመለዋወጥ እና ከሕዝቡ ጋር በመተባበር እየሠራ ነው ብለዋል።
በምርጫ ዕለት እንዲሁም ከምርጫ በኋላ ባሉት ሂደቶች ሰላምን ለማስከበር አስፈላጊው የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ ዝግጅት መደረጉ ይፋ ተደርጓል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል በሀገር አቀፍ ደረጃ የተደረጉ የምርጫ ዝግጅቶችን የገመገመ ከፍተኛ ስብሰባ ካካሄደ በኋላ፤ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን ለማረጋገጥ ቁርጠኛ እንደሆነ አረጋግጧል።
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፤ "የምርጫውን ሒደት ለማስተጓጎል በተለያዩ አካላት የተደረጉ ሙከራዎች በመከላከያ ሠራዊቱና በሌሎች የፀጥታ አካላት የተቀናጀ እርምጃ ሙሉ በሙሉ እንዲከሽፉ ተደርገዋል" ሲሉ ተናግረዋል።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በበኩላቸው፤ ግብረ-ኃይሉ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር መረጃዎችን በመለዋወጥ እና ከሕዝቡ ጋር በመተባበር እየሠራ ነው ብለዋል።
በምርጫ ዕለት እንዲሁም ከምርጫ በኋላ ባሉት ሂደቶች ሰላምን ለማስከበር አስፈላጊው የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ ዝግጅት መደረጉ ይፋ ተደርጓል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X