በዛፖሮዢያ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ላይ የሚፈጸሙ የዩክሬን ጥቃቶች የጨረር አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ ተባለ
12:06 31.05.2026 (የተሻሻለ: 12:35 31.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በዛፖሮዢያ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ላይ የሚፈጸሙ የዩክሬን ጥቃቶች የጨረር አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ ተባለ
በኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት፤ ከወታደራዊ ግቦች ስሌት ባለፈ ሰፊ የራዲዮአክቲቭ ጥፋት የመፍጠር አደጋ አለው ሲሉ የጣቢያው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኢቭጌኒያ ያሺና አስጠንቅቀዋል።
ያሺና ለስፑትኒክ በሰጡት አስተያየት፤ “ጉዳቱ በኒውክሌር ማብላያዎቹ ወይም በተርባይን ክፍሉ ላይ ይድረስ፤ እንዲህ ዓይነቶቹ ጥቃቶች ከወታደራዊ እርምጃዎች ያለፉ ናቸው” ብለዋል።
የጣቢያው ደጋፊ ሥርዓቶች ከወደሙ ከቁጥጥር ውጪ የነዳጅ መጋል፣ የራዲየሽን ልቀት እና ሰፊ ግዛቶችን የመበከል አደጋ ሊያስከትል ይችላል። “ከጦር ሜዳው ባሻገር ሰፊ መዘዝ ይኖረዋል” ሲሉም አክለዋል።
የዩክሬን የጦር ድሮን በዛፖሮዢያ የኒውክሌር ኃይል ጣቢያ የኃይል ማመንጫ ቁጥር 6 ተርባይን ክፍል ሕንጻ ላይ ጥቃት ማድረሱን የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሊካቾቭ ቅዳሜ ምሽት ገልጸዋል።
በደረሰው ጥቃት የሰው ሕይወት እንዳልጠፋ፣ ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰ እና የቴክኖሎጂ ሂደቶች ላይ መስተጓጎል እንዳልተፈጠረ እንዲሁም ራዲየሽኑ በተለመደው መጠን ላይ እንደሚገኘ የጣቢያው የፕሬስ አገልግሎት አስታውቋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
በኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት፤ ከወታደራዊ ግቦች ስሌት ባለፈ ሰፊ የራዲዮአክቲቭ ጥፋት የመፍጠር አደጋ አለው ሲሉ የጣቢያው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኢቭጌኒያ ያሺና አስጠንቅቀዋል።
ያሺና ለስፑትኒክ በሰጡት አስተያየት፤ “ጉዳቱ በኒውክሌር ማብላያዎቹ ወይም በተርባይን ክፍሉ ላይ ይድረስ፤ እንዲህ ዓይነቶቹ ጥቃቶች ከወታደራዊ እርምጃዎች ያለፉ ናቸው” ብለዋል።
የጣቢያው ደጋፊ ሥርዓቶች ከወደሙ ከቁጥጥር ውጪ የነዳጅ መጋል፣ የራዲየሽን ልቀት እና ሰፊ ግዛቶችን የመበከል አደጋ ሊያስከትል ይችላል። “ከጦር ሜዳው ባሻገር ሰፊ መዘዝ ይኖረዋል” ሲሉም አክለዋል።
የዩክሬን የጦር ድሮን በዛፖሮዢያ የኒውክሌር ኃይል ጣቢያ የኃይል ማመንጫ ቁጥር 6 ተርባይን ክፍል ሕንጻ ላይ ጥቃት ማድረሱን የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሊካቾቭ ቅዳሜ ምሽት ገልጸዋል።
በደረሰው ጥቃት የሰው ሕይወት እንዳልጠፋ፣ ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰ እና የቴክኖሎጂ ሂደቶች ላይ መስተጓጎል እንዳልተፈጠረ እንዲሁም ራዲየሽኑ በተለመደው መጠን ላይ እንደሚገኘ የጣቢያው የፕሬስ አገልግሎት አስታውቋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X