ሩሲያ የሳኅል ቀጣናን ሽብርተኝነት በመዋጋት ረገድ 'ሁነኛ አጋር' ናት - ኒጀራዊ የፖለቲካ ሳይንስ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

ሩሲያ የሳኅል ቀጣናን ሽብርተኝነት በመዋጋት ረገድ 'ሁነኛ አጋር' ናት - ኒጀራዊ የፖለቲካ ሳይንስ ባለሙያ

በሳኅል ቀጣና ያለው የሽብር ቡድኖች እንቅስቃሴ ለመላው አኅጉር እና ባሻገር አሉታዊ መዘዞች ሊኖሩት እንደሚችል አብዱላሂ ኢድሪሳ ጃምስ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

“ሽብርተኝነት በተለይም በአውሮፓ ኃያላን እና የዩክሬን ተሳትፎ አዲስ መልክ እየያዘ መጥቷል። ይህ ድርጊት አስቀድሞ በሳኅል ሀገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተወግዟል። በማሊ የተፈጸመው ጥቃት የውጭ ጣልቃ ገብነቶቹን መጠን ያየንበት ነው።”

ሩሲያ በመረጃ ልውውጥ፣ የወታደራዊ መሣሪያዎችን በማቅረብ እና እንዲሁም በማሊ የአፍሪካ ኮር በታየው ተጨባጭ ተግባራዊ እገዛ ይህንን ስጋት ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ስልታዊ አጋር ሆናለች ሲሉም ባለሙያው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0