ቢያንስ አምስት ሰዎች ከኢቦላ ድነዋል - የኮንጎ ሚኒስትር
08:56 31.05.2026 (የተሻሻለ: 09:04 31.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ቢያንስ አምስት ሰዎች ከኢቦላ ድነዋል - የኮንጎ ሚኒስትር
የሕዝብ ጤና ሚኒስትር ሮጀር ካምባ፤ ስለታካሚዎች ዝርዝር መረጃ ሳይሰጡ እሁድ ወይም ሰኞ አምስት ሰዎች ማገገማቸው ሊገለጽ እንደሚችል ለመገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።
ያሉበት የጤና ሁኔታ ተስፋ ሰጪ ነው ሲሉም አክለዋል።
እስካሁን 1,028 የተጠረጠሩ ሰዎች መመዝገባቸውን እና ከእነዚህ ውስጥ 225ቱ መረጋገጡን እንዲሁም በቁጥሩ ላይ "ምንም ዓይነት ጭማሪ እንዳልታየ" ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
በኢቦላ የተያዘው የመጀመሪያ ታካሚ ሙሉ በሙሉ አገግሞ ረቡዕ ከህክምና ማዕከል እንደወጣ የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለሥልጣን ቀደም ሲል ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X