- Sputnik አፍሪካ, 1920
Turning Africa Forward
በአህጉሪቱ ስልታዊ መነቃቃት ላይ ግልጽ እይታን የሚሰጥ በስፑትኒክ አፍሪካ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ፕሮግራም ። ከዜናዎች ባሻገር፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላትን እየተለወጠ የመጣ ሚና በጥልቀት ይተነትናል፤ የወደፊቱን የዓለም ሥርዓት በመቅረጽ ረገድ ያለውን አቅጣጫ በሰፊው ይዳስሳል።

የቶጎ ታሪካዊ የቪዛ ስረዛ ከአፍሪካውያን የጋራ እጣ ፈንታ አንጻር

የቶጎ ታሪካዊ የቪዛ ስረዛ ከአፍሪካውያን የጋራ እጣ ፈንታ አንጻር
ሰብስክራይብ
''አፍሪካውያን በገዛ አህጉራቸው በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ እና ሀብታቸውን፣ እውቀታቸውንና አቅማቸውን እንዲያስተሳስሩ መፍቀድ የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው ። ቶጎ የወሰደችው የድንበር መክፈት ውሳኔ፣ አህጉራዊ ትብብርን ከተራ የፖለቲካ መግለጫዎች ባለፈ በተግባር ማረጋገጥ እንደሚቻል ያሳየ ደማቅ የአንድነት ማሳያ ነው'' ሲሉ የዘላቂ ቱሪዝም ተንታኝ ጁዲ ኬፐር-ጎና ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል ።
በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስታችን፤ የምዕራባውያንን ተጽዕኖ እና የቅኝ ግዛት የድንበር ከፋፋይ አጥርን በተግባር ስለሰበረው የቶጎ ታሪካዊ የቪዛ ነፃ ፖሊሲ በሰፊው እንወያያለን ። ፕሮግራማችን ትኩረቱን የሚያደርገው የአፍሪካ ሀገራት በጋራ በመቆም የራሳቸውን መዋቅራዊ ሉዓላዊነት እንዴት ማጠናከር ይችላሉ በሚለው ላይ ነው ።
ጠንካራ የአፍሪካ-ለአፍሪካ የጉዞ እና የንግድ ትስስር መፍጠር ስለሚቻልበት ሁኔታ ፣ አህጉራዊ ካፒታል ወደ ውጭ ሀገራት የኦንላይን ፕላትፎርሞች እንዳይፈስ ለመግታት ወጣት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችን በጋራ ስለማብቃት ፣ እንዲሁም የኢኮኖሚ ስኬታችንን በምዕራባውያን መለኪያ ሳይሆን በአፍሪካውያን ማህበረሰቦች የጋራ ተጠቃሚነት እና ሁለንተናዊ ደህንነት ለመለካት በሚያስችሉ አዳዲስ መዋቅሮች ዙሪያ ከኬንያዊቷ የቱሪዝም ባለሙያ ጁዲ ኬፐር-ጎና ጋር በጥልቀት ተወያይተናል ።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0