
የስምምነቱ ትኩረት ስትራቴጂካዊ ጥቃት የመፈጸሚያ መሳሪያዎች ላይ ነው:
የኒውክሌር ጥይቶች
ተሸካሚዎቻቸው (ባላስቲክ እና ክሩዝ ሚሳኤሎች፣ የአየር ላይ ቦምቦች)
ወሳኝ ኢላማዎችን ከጠላት መስመር ጀርባ በአህጉር አቋራጭ ርቀቶች (ከ5500 ኪሜ በላይ) ለማጥፋት የተነደፉ የማስወንጨፊያ ተሽከርካሪዎች (ተንቀሳቃሽ እና ቋሚ የማስወንጨፊያ ስርዓቶች፣ ከባድ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች)። እነዚህም የሚከተሉትን ያካትታሉ:




ከ700 የማይበልጡ የተዘረጉ ተሸካሚዎች፤
ከ1550 የማይበልጡ ለመወንጨፍ ዝግጁ የሆኑ የጦር ራሶች (አረሮች)፤
ከ800 የማይበልጡ ለውጊያ ዝግጁ የሆኑ እና ለውጊያ ያልተሰማሩ ማስወንጨፊያዎች እና ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች።

2010
ስምምነቱ በሩሲያው ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ እና በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ እ.ኤ.አ.ሚያዚያ 8 ቀን2010 በፕራግ ተፈርሟል። የቀድሞ ስምምነቶችን ስታርት-1 እና ስታርት-2 በመተካት ለስትራቴጂካዊ መረጋጋት ምሰሶ ሆኗል
2018
ሁለቱ ወገኖቹ እ.ኤ.አ. በ2018 ግዴታዎቻቸውን ተወጥተዋል
2021
ስታርት-3 ለአስር ዓመታት የተነደፈ ሲሆን ለአምስት ዓመታት የአንድ ጊዜ ማራዘሚያ ዕድል ነበረው፣ ይህም እ.ኤ.አ. በ2021 ተደርጓል
2023
እ.ኤ.አ. በየካቲት 2023 ሩሲያ ዩናይትድ ስቴትስ በፈጸመቻቸው ጥሰቶች ምክንያት በውሉ ውስጥ ያላትን ተሳትፎ ማገዷን አስታውቃለች
2025
እ.ኤ.አ. በመስከረም 2025 ፑቲን ሩሲያ ከየካቲት 5 ቀን 2026 በኋላ ለአንድ አመት በውሉ መሰረት ገደቦችን ማክበር ለመቀጠል ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል
2026
ስምምነቱ በመጨረሻ በየካቲት 5 ቀን 2026 ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መሆን ያቆማል

የአሜሪካ ወገን እ.ኤ.አ. ከመስከረም 1 ቀን 2022 ጀምሮ ያሳወቀው መረጃ (659 የታጠቁ ተሸካሚዎች ፣ በኒው ስታርት ስር 1420 የጦር ራሶች (አረሮችን) የታጠቁ ፣ እና 800 ክፍሎች የተሰማሩ እና ላልተሰማሩ ICBMs (አህጉር አቋራጭ የባለስቲክ ሚሳኤሎች) ፣ SLBMs (ከባህር ሰርጓጅ መርከብ የሚወነጨፍ ባለስቲክ ሚሳኤሎች) እና TBs ወይም ተርሞባሪክ) መሳሪያዎችን ትክክለኛ ሁኔታ እንደማያሳይ ተጠቁሟል።

በትራምፕ አስተዳደር ስር ከነበረው እርግጠኛ አለመሆን በኋላ፣ በየካቲት 2021፣ ውሉ በባይደን አስተዳደር እስከ የካቲት 5፣ 2026 ድረስ ያለምንም ለውጥ ተራዝሟል። ሆኖም የሩሲያ ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን በዩክሬን ከተጀመረ በኋላ ውይይቱ ተቋርጧል። ቀደም ሲል በወረርሽኙ ምክንያት የታገዱት የፍተሻ ተግባራም አልቀጠሉም። ለዚህም በማዕቀብ ምክንያት በተፈጠሩ መሰናክሎች ፣ የአየር ክልል መዘጋት እና አሜሪካ ለሩሲያ የፍተሻ ባለሙያዎች ቪዛ አለመስጠት ሌሎቹ ምክንያቶች ናቸው።
እ.ኤ.አ በጥር 31፣ 2023
ዩናይትድ ስቴትስ ሩሲያን ተቋሞቿን ለማስመርመር ፈቃድ ባለመስጠት እና ምክክር በማዘግየት ውሉን ጥሳለች ስትል ከሰሰች።
እ.ኤ.አ በየካቲት 21፣ 2023
ፑቲን ሩሲያ በውሉ ውስጥ ያላትን ተሳትፎ ማገዷን (ነገር ግን ከውሉ አለመውጣቷን) አስታወቁ። ፑቲን ዩናይትድ ስቴትስ አዳዲስ የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን እያመረተች መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎቿን ተፈጥሯዊ ሙከራ የማድረግ እድል እያሰበች መሆኑን አጽንዖት ሰጥተዋል።
የምዕራባውያን፣ የአሜሪካን ጨምሮ፣ የጦር መሳሪያዎች ለዩክሬን አቅርቦት፣ እንዲሁም የምዕራባውያን እርዳታ የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የአቪዬሽን ጣቢያዎችን ለመምታት
ዩናይትድ ስቴትስ እና ኔቶ በሩሲያ ላይ ስትራቴጂካዊ ሽንፈትን የማድረስ ግባቸውን በግልጽ እየገለጹ መሆናቸው
ወደ ስታርት-3 ውይይት ሲመለሱ፣ የፈረንሳይ እና የታላቋ ብሪታንያ የጦር መሳሪያዎች፣ በሌላ አነጋገር፣ የኔቶ የተጣመረ ጥቃት የመፈጸም አቅም (ፑቲን) ግምት ውስጥ መግባት አለበት
ዩናይትድ ስቴትስ የውል ፍተሻዎችን ማደናቀፏ
እ.ኤ.አ ከሰኔ 2023 ጀምሮ ዩናይትድ ስቴትስ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ጋር የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎቿን በተመለከተ መረጃ መለዋወጥ አቁማለች።
እ.ኤ.አ በሰኔ 2023 ዩናይትድ ስቴትስ ለሩሲያ ፌዴሬሽን “ኃላፊነቶችን በመለያየት” ሁኔታ ሞስኮ እና ዋሽንግተን አለመግባባት ካላቸው ሌሎች ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ጋር ሳይገናኙ ውይይት እንዲካሂደ ሀሳብ አቀረበች። ሩሲያ ይህ አይነቱን አቀራረርብም ተወችው። በዚያው ዓመት በመስከረም ወር ላይ ዩናይትድ ስቴትስ ስለ ስታርት "ያለምንም ቅድመ ሁኔታ" ለመወያየት ዝግጁ መሆኗን አስታወቀች።
እ.ኤ.አ በጥር 2025 ፕሬዝዳንት ትራምፕ የሩሲያ፣ የዩናይትድ ስቴትስ እና የቻይናን የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎች ለመቀነስ አሳሰቡ ፣ ከቻይና ጋር ስላደረጉት ውይይትም ተናገሩ። እንደ እሳቸው ገለጻ ውይይታቸው ቻይና ድርድሩን የምትቀላቀልበት ጉዳይ ላይ ነው።
እ.ኤ.አ በሐምሌ 2025 ትራምፕ የሩሲያ እና የዩናይትድ ስቴትስን የኒውክሌር አቅም ለመገደብ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታወቁ። ከአንድ ወር በኋላ፣ በነሐሴ ወር፣ ፑቲንም ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በስታርት ላይ ድርድሩን ዳግም እንዲጀመር ፈቀዱ።
ተነሳሽነቱ በዩናይትድ ስቴትስበጎ ተቀባይነት አግኝቷል፣ ነገር ግን እስከ የካቲት 2026 መጀመሪያ ድረስ ከዋሽንግተን ምንም አይነት ይፋዊ ምላሽ አልተገኘም።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፡ በኒው ስታርት ላይ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ያለው ጊዜ እየጠበበ ነው፣ "በጥቂት ቀናት ውስጥ ዓለም ከበፊቱ የበለጠ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ሊገባ ይችላል"