An unarmed Minuteman III intercontinental ballistic missile launches during an operational test on Wednesday, May 1, 2019, at Vandenberg Air Force Base, Calif - Sputnik አፍሪካ

የ’ኒው ስታርት’ ስምምነት፡ አሜሪካ እና ሩሲያ የኑክሌር ገደብ ለማበጀት የሄዱበት መንገድ

‘ኒው ስታርት’ ምንድን ነው?
ኒው ስታርት የሩሲያ እና አሜሪካ ስምምነት ሲሆን የሁለቱ አገሮች የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎች መጠን የሚቆጣጠር ስምምነት ነው። ስሙም ስትራቴጂካዊ የጦር መሳሪያዎች ቅነሳ ስምምነት (Strategic Arms Reductions Treaty) የሚል ምህጻረ ቃል ነው።
‘ኒው ስታርት' ስምምነት በዝርዝር
በ ‘ኒው ስታርት’ ገደብ የተጣለባቸው የትኞቹ የጦር መሳሪያዎች ናቸው?

የስምምነቱ ትኩረት ስትራቴጂካዊ ጥቃት የመፈጸሚያ መሳሪያዎች ላይ ነው:

1

የኒውክሌር ጥይቶች

2

ተሸካሚዎቻቸው (ባላስቲክ እና ክሩዝ ሚሳኤሎች፣ የአየር ላይ ቦምቦች)

3

ወሳኝ ኢላማዎችን ከጠላት መስመር ጀርባ በአህጉር አቋራጭ ርቀቶች (ከ5500 ኪሜ በላይ) ለማጥፋት የተነደፉ የማስወንጨፊያ ተሽከርካሪዎች (ተንቀሳቃሽ እና ቋሚ የማስወንጨፊያ ስርዓቶች፣ ከባድ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች)። እነዚህም የሚከተሉትን ያካትታሉ:

• አህጉር አቋራጭ ባላስቲክ ሚሳኤሎች (የአሜሪካ ሚኒትማን II-III፣ ፒስኪፐር፣ የሩሲያ የ"ቶፖል" ቤተሰብ ሚሳኤል ስርዓቶች፣ ፈሳሽ ነዳጅ የሚጠቀሙ አህጉር አቋራጭ ባላስቲክ ሚሳኤሎች፣ አር-36ኤም፣ አራኤስ-24 ያርስ)፣ ማስወንጨፊያዎቻቸው እና የጦር ራስ (አረር)
• ከባህር ሰርጓጅ መርከብ የሚወነጨፉ ባላስቲክ ሚሳኤሎች እና ተሸካሚዎቻቸው (የአሜሪካ ትራይደንት-II እና የሩሲያ አር-29አር፣ አር-39፣ አር-39አርኤም እና አር-30)
• የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን መሸከም የሚችሉ ከባድ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች (የሩሲያ ቲዩ- 95 ኤማኤስ እና ቲዩ-160፣ የአሜሪካ ቢ-52ጂ፣ ቢ-52ኤች፣ ቢ-1ቢእና ቢ-2ኤ)።
ስምምነቱግልጽ ገደቦችን አስቀምጧል:
1

ከ700 የማይበልጡ የተዘረጉ ተሸካሚዎች፤

2

ከ1550 የማይበልጡ ለመወንጨፍ ዝግጁ የሆኑ የጦር ራሶች (አረሮች)፤

3

ከ800 የማይበልጡ ለውጊያ ዝግጁ የሆኑ እና ለውጊያ ያልተሰማሩ ማስወንጨፊያዎች እና ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች።

በዚህ ስምምነት የተሳታፉት ወገኖች የኑክሌር‘ትራያድ’ (የመሬት ፣ ባህር ሰርጓጅ እና የአየር ) አካላትን በራሳቸው በነፃነት የሚያወጡትን መጠን ለመወሰን ተፈቅዶላቸው። ስምምነቱ ታክቲካል የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን፣ የሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶችን እና የኒውክሌር ያልሆኑ ስትራቴጂካዊ መሳሪያዎችን (ለምሳሌ ሃይፐርሶኒክ ሚሳኤሎችን) አላካተተም።
ክትትሉ የተካሄደው በሁለትዮሽ አማካሪ ኮሚሽን እና በቁጥጥር ስርዓቱ አማካይነት ነው።
የስምምነቱ አጭር ታሪክ
የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ እና የቀድሞ የሩሲያ ፕሬዚዳንት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ አዲሱን የስታርት ስምምነት እ.ኤ.አ ሚያዝያ 8 ቀን 2010 ዓ.ም በፕራግ ካስል ከፈረሙ በኋላ። - Sputnik አፍሪካ
የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ እና የቀድሞ የሩሲያ ፕሬዚዳንት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ አዲሱን የስታርት ስምምነት እ.ኤ.አ ሚያዝያ 8 ቀን 2010 ዓ.ም በፕራግ ካስል ከፈረሙ በኋላ።

2010

ስምምነቱ በሩሲያው ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ እና በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ እ.ኤ.አ.ሚያዚያ 8 ቀን2010 በፕራግ ተፈርሟል። የቀድሞ ስምምነቶችን ስታርት-1 እና ስታርት-2 በመተካት ለስትራቴጂካዊ መረጋጋት ምሰሶ ሆኗል

2018

ሁለቱ ወገኖቹ እ.ኤ.አ. በ2018 ግዴታዎቻቸውን ተወጥተዋል

2021

ስታርት-3 ለአስር ዓመታት የተነደፈ ሲሆን ለአምስት ዓመታት የአንድ ጊዜ ማራዘሚያ ዕድል ነበረው፣ ይህም እ.ኤ.አ. በ2021 ተደርጓል

2023

እ.ኤ.አ. በየካቲት 2023 ሩሲያ ዩናይትድ ስቴትስ በፈጸመቻቸው ጥሰቶች ምክንያት በውሉ ውስጥ ያላትን ተሳትፎ ማገዷን አስታውቃለች

2025

እ.ኤ.አ. በመስከረም 2025 ፑቲን ሩሲያ ከየካቲት 5 ቀን 2026 በኋላ ለአንድ አመት በውሉ መሰረት ገደቦችን ማክበር ለመቀጠል ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል

2026

ስምምነቱ በመጨረሻ በየካቲት 5 ቀን 2026 ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መሆን ያቆማል

የውሉ አፈጻጸም በተዋዋይ ወገኖች እና የአሜሪካ ጥሰቶች
እ.ኤ.አ. በ2018 የሩሲያ ፌዴሬሽን ገደቦችን አሟልታ፣ የጦር መሳሪያ ክምችቷን ከተቀመጡት ደረጃዎች በታች ቀንሳ ነበር። የሩሲያ አጠቃላይ ስትራቴጂካዊ የማጥቃት ሚሳኤል አቅም የሚከተለው ነበር:
• 527 ክፍሎች ለተሰማሩ አህጉር አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳኤሎች እና ከባህር ሰርጓጅ መርከብ የሚወነጨፉ እና ከባድ ቦምብ ጣይ ባሊስቲክ ሚሳኤሎች
• 1444 ክፍሎች በእነሱ ላይ ለተጫኑ የጦር ራሶች እንዲሁም የኒውክሌር ጦር ራሶች (አረሮች)
• 779 ክፍሎች ለተሰማሩ እና ላልተሰማሩ አህጉር አቀፍ የባላስቲክ ሚሳኤሎች እና በባህር ሰርጓጅ ውስጥ ለተተኮሱ ባለስቲክ ሚሳኤሎች፣ ለተሰማሩ እና ላልተሰማሩ ከባድ ቦምቦ ጣይ አዉሮፕላኖች
ዩናይትድ ስቴትስም የተስማማችባቸውን አጠቃላይ የስትራቴጂካዊ የጥቃት መፈጸሚያ መሳሪያዎች ብዛት (የቁጥር መጠን) ማሳካቷን አስታውቃለች፣ ነገር ግን ይህንን ያደረገችው "ተቀይረዋል" ተብለው የተገለጹትን አንዳንድ የጦር መሳሪያዎች ከቁጥር ውስጥ በህገወጥ መንገድ በማስወጣት ነው። እየተነጋገርን ያለነው ስለ 56 ትራይደንት-II SLBM (ከባህር ሰርጓጅ መርከብ የሚወነጨፍ ባለስቲክ ሚሳኤል) ማስወንጨፊያዎች እና 41 -52 ኤች ከባድ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች ነው። ይህ እንደ ሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጻ፣ በጦር ተሸካሚዎች ላይ በአጓጓዦች ላይ ያለውን ገደብ በ101 ክፍሎች እንዲበልጥ አድርጓል።
የአሜሪካ አየር ኃይል ቢ-52 ቦምብ ጣይ አውሮፕላን 'አይረን ዎልፍ 2016' በተባለ ወታደራዊ ልምምድ ወቅት በፓብራዴ የስልጠና ክልል ላይ ሲበር  - Sputnik አፍሪካ
የአሜሪካ አየር ኃይል ቢ-52 ቦምብ ጣይ አውሮፕላን 'አይረን ዎልፍ 2016' በተባለ ወታደራዊ ልምምድ ወቅት በፓብራዴ የስልጠና ክልል ላይ ሲበር

የአሜሪካ ወገን እ.ኤ.አ. ከመስከረም 1 ቀን 2022 ጀምሮ ያሳወቀው መረጃ (659 የታጠቁ ተሸካሚዎች ፣ በኒው ስታርት ስር 1420 የጦር ራሶች (አረሮችን) የታጠቁ ፣ እና 800 ክፍሎች የተሰማሩ እና ላልተሰማሩ ICBMs (አህጉር አቋራጭ የባለስቲክ ሚሳኤሎች) ፣ SLBMs (ከባህር ሰርጓጅ መርከብ የሚወነጨፍ ባለስቲክ ሚሳኤሎች) እና TBs ወይም ተርሞባሪክ) መሳሪያዎችን ትክክለኛ ሁኔታ እንደማያሳይ ተጠቁሟል።

የቻይና አቋም በ ስታርት-3
ቻይና የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ክምችቷ እጅግ በጣም ያነሰ መሆኑን በመጥቀስ ስምምነቱን ለመቀላቀል ፈቃደኛ አልሆነችም። ቤጂንግ የተሳትፎን ጉዳይ ለመመልከት ዝግጁ የሆነችው የሩሲያ እና የዩናይትድ ስቴትስ የኒውክሌር አቅም ወደ ቻይና ደረጃ ዝቅ ካለ ፣ ማለትም 20 እጥፍ ከተቀነሰ በኋላ ብቻ ነው።
እ.ኤ.አ በመስከረም 3 ቀን 2015 በቤጂንግ ከተካሄደው ወታደራዊ ሰልፍ በኋላ የታየው በቅርቡ የተሻሻለው የቻይናው ዲኤፍ-5ቢ አህጉር አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳኤል የላይኛው ክፍል - Sputnik አፍሪካ
እ.ኤ.አ በመስከረም 3 ቀን 2015 በቤጂንግ ከተካሄደው ወታደራዊ ሰልፍ በኋላ የታየው በቅርቡ የተሻሻለው የቻይናው ዲኤፍ-5ቢ አህጉር አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳኤል የላይኛው ክፍል
የውሉ መራዘም እና ቀውሱ

በትራምፕ አስተዳደር ስር ከነበረው እርግጠኛ አለመሆን በኋላ፣ በየካቲት 2021፣ ውሉ በባይደን አስተዳደር እስከ የካቲት 5፣ 2026 ድረስ ያለምንም ለውጥ ተራዝሟል። ሆኖም የሩሲያ ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን በዩክሬን ከተጀመረ በኋላ ውይይቱ ተቋርጧል። ቀደም ሲል በወረርሽኙ ምክንያት የታገዱት የፍተሻ ተግባራም አልቀጠሉም። ለዚህም በማዕቀብ ምክንያት በተፈጠሩ መሰናክሎች ፣ የአየር ክልል መዘጋት እና አሜሪካ ለሩሲያ የፍተሻ ባለሙያዎች ቪዛ አለመስጠት ሌሎቹ ምክንያቶች ናቸው።

የሩሲያ ተሳትፎዋን ማቋረጥና ምክንያቶቹ

እ.ኤ.አ በጥር 31፣ 2023

ዩናይትድ ስቴትስ ሩሲያን ተቋሞቿን ለማስመርመር ፈቃድ ባለመስጠት እና ምክክር በማዘግየት ውሉን ጥሳለች ስትል ከሰሰች።

እ.ኤ.አ በየካቲት 21፣ 2023

ፑቲን ሩሲያ በውሉ ውስጥ ያላትን ተሳትፎ ማገዷን (ነገር ግን ከውሉ አለመውጣቷን) አስታወቁ። ፑቲን ዩናይትድ ስቴትስ አዳዲስ የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን እያመረተች መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎቿን ተፈጥሯዊ ሙከራ የማድረግ እድል እያሰበች መሆኑን አጽንዖት ሰጥተዋል።

ፕሬዚዳንት ፑቲን ሩሲያ ከአዲሱ የ ስታርት ስምምነት መውጣቷን ሲያስታዉቁ
ለማገድ የተሰጡምክንያቶች፦
1

የምዕራባውያን፣ የአሜሪካን ጨምሮ፣ የጦር መሳሪያዎች ለዩክሬን አቅርቦት፣ እንዲሁም የምዕራባውያን እርዳታ የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የአቪዬሽን ጣቢያዎችን ለመምታት

2

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኔቶ በሩሲያ ላይ ስትራቴጂካዊ ሽንፈትን የማድረስ ግባቸውን በግልጽ እየገለጹ መሆናቸው

3

ወደ ስታርት-3 ውይይት ሲመለሱ፣ የፈረንሳይ እና የታላቋ ብሪታንያ የጦር መሳሪያዎች፣ በሌላ አነጋገር፣ የኔቶ የተጣመረ ጥቃት የመፈጸም አቅም (ፑቲን) ግምት ውስጥ መግባት አለበት

4

ዩናይትድ ስቴትስ የውል ፍተሻዎችን ማደናቀፏ

ሩሲያ በውሉ ውስጥ ያላትን ተሳትፎ ካገደች በኋላ የዩናይትድ ስቴትስ ድርጊቶች
1

እ.ኤ.አ ከሰኔ 2023 ጀምሮ ዩናይትድ ስቴትስ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ጋር የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎቿን በተመለከተ መረጃ መለዋወጥ አቁማለች።

2

እ.ኤ.አ በሰኔ 2023 ዩናይትድ ስቴትስ ለሩሲያ ፌዴሬሽን “ኃላፊነቶችን በመለያየት” ሁኔታ ሞስኮ እና ዋሽንግተን አለመግባባት ካላቸው ሌሎች ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ጋር ሳይገናኙ ውይይት እንዲካሂደ ሀሳብ አቀረበች። ሩሲያ ይህ አይነቱን አቀራረርብም ተወችው። በዚያው ዓመት በመስከረም ወር ላይ ዩናይትድ ስቴትስ ስለ ስታርት "ያለምንም ቅድመ ሁኔታ" ለመወያየት ዝግጁ መሆኗን አስታወቀች።

3

እ.ኤ.አ በጥር 2025 ፕሬዝዳንት ትራምፕ የሩሲያ፣ የዩናይትድ ስቴትስ እና የቻይናን የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎች ለመቀነስ አሳሰቡ ፣ ከቻይና ጋር ስላደረጉት ውይይትም ተናገሩ። እንደ እሳቸው ገለጻ ውይይታቸው ቻይና ድርድሩን የምትቀላቀልበት ጉዳይ ላይ ነው።

4

እ.ኤ.አ በሐምሌ 2025 ትራምፕ የሩሲያ እና የዩናይትድ ስቴትስን የኒውክሌር አቅም ለመገደብ ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታወቁ። ከአንድ ወር በኋላ፣ በነሐሴ ወር፣ ፑቲንም ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በስታርት ላይ ድርድሩን ዳግም እንዲጀመር ፈቀዱ።

አሁን ያለው ሁኔታ እና ተስፋዎች
እ.ኤ.አ በመሰከረም 2025 ቭላድሚር ፑቲን ሩሲያ ስምምነቱ ካለቀ በኋላ (የካቲት 5፣ 2026) ለአንድ አመት ገደቦቿን ለማክበር ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል፣ ነገር ግን ከዩናይትድ ስቴትስ የጋራ ምላሽ ካለ ብቻ ነው።
እ.ኤ.አ መስከረም 22, 2025፣ ፑቲን ሩሲያ የ ስታርት ስምምነት ገደቦችን ለተጨማሪ አንድ ዓመት ለመጠበቅ ዝግጁ መሆኗን ሲናገሩ

ተነሳሽነቱ በዩናይትድ ስቴትስበጎ ተቀባይነት አግኝቷል፣ ነገር ግን እስከ የካቲት 2026 መጀመሪያ ድረስ ከዋሽንግተን ምንም አይነት ይፋዊ ምላሽ አልተገኘም።

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፡ በኒው ስታርት ላይ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ያለው ጊዜ እየጠበበ ነው፣ "በጥቂት ቀናት ውስጥ ዓለም ከበፊቱ የበለጠ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ሊገባ ይችላል"

ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ራያብኮቭ የ ‘ኒው ስታርት’ ቀውስ መንስኤዎች ላይ ንግግር ሲያደርጉ
Go back to the beginningGo back to the main page
አዳዲስ ዜናዎች
0