СВО - Sputnik አፍሪካ

የልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን መነሻ፤ የዩክሬን ግጭት ታሪክ

መፈንቅለ መንግሥት
እ.አ.አ በህዳር 2013 የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቪክቶር ያኑኮቪች ከሩሲያ ጋር ያለው ግንኙነት እንዳይቋረጥ በመፍራት ከአውሮፓ ህብረት ጋር የትብብር ስምምነትን ለመፈረም አሻፈረኝ አሉ። ይህ ውሳኔ በኪዬቭ መጠነ ሰፊ ተቃውሞ አስነሳ።
በፀጥታ ኃይሎች እና በአብዛኛው አክራሪ ብሔርተኞች በሆኑ ተቃዋሚዎች መካከል ለወራት የዘለቀው ፍጥጫ፤ ዩሮሜይዳን በመባል የሚታወቀው ክስተት፤ በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሞት እና መፈንቅለ መንግሥት አስከትሏል።
እ.አ.አ የካቲት 22 ምሽት ዩሮሜይዳን አክቲቪስቶች ፓርላማውን፣ የፕሬዝዳንቱን ፅ/ቤት እና የመንግሥት ህንፃዎችን ተቆጣጠሩ። መፈንቅለ መንግሥቱንም ተከትሎ ሥልጣኑ ወደ ተቃዋሚዎች እጅ ገባ። ሕጋዊው ፕሬዝዳንት ቪክቶር ያኑኮቪች በአስቸኳይ ወደ ሩሲያ ለመሸሽ ተገደዱ።
የፖሊስ አባላት በኪየቭ በሚገኘው ማይዳን ነዛሌዥኖስቲ አደባባይ ላይ ይታያሉ፣ እዚያም በተቃዋሚዎችና በፖሊስ መካከል ግጭት ተቀስቅሷል - Sputnik አፍሪካ
የፖሊስ አባላት በኪየቭ በሚገኘው ማይዳን ነዛሌዥኖስቲ አደባባይ ላይ ይታያሉ፣ እዚያም በተቃዋሚዎችና በፖሊስ መካከል ግጭት ተቀስቅሷል
የፖሊስ አባላት በኪየቭ መሃል ከተማ በተካሄደው ግጭት ወቅት - Sputnik አፍሪካ
የፖሊስ አባላት በኪየቭ መሃል ከተማ በተካሄደው ግጭት ወቅት
የአውሮፓ ህብረት ውህደት ደጋፊ ሰልፎች ተሳታፊ በኪየቭ ግሩሼቭስኮጎ ጎዳና ላይ ይታያል - Sputnik አፍሪካ
የአውሮፓ ህብረት ውህደት ደጋፊ ሰልፎች ተሳታፊ በኪየቭ ግሩሼቭስኮጎ ጎዳና ላይ ይታያል
ፖሊስ አባላት በኪየቭ በሚገኘው ማይዳን ነዛሌዥኖስቲ አደባባይ ላይ ይታያሉ፣ በዚያም በተቃዋሚዎችና በፖሊስ መካከል ግጭት ተቀስቅሷል - Sputnik አፍሪካ
ፖሊስ አባላት በኪየቭ በሚገኘው ማይዳን ነዛሌዥኖስቲ አደባባይ ላይ ይታያሉ፣ በዚያም በተቃዋሚዎችና በፖሊስ መካከል ግጭት ተቀስቅሷል
1.
የፖሊስ አባላት በኪየቭ በሚገኘው ማይዳን ነዛሌዥኖስቲ አደባባይ ላይ ይታያሉ፣ እዚያም በተቃዋሚዎችና በፖሊስ መካከል ግጭት ተቀስቅሷል
2.
የፖሊስ አባላት በኪየቭ መሃል ከተማ በተካሄደው ግጭት ወቅት
3.
የአውሮፓ ህብረት ውህደት ደጋፊ ሰልፎች ተሳታፊ በኪየቭ ግሩሼቭስኮጎ ጎዳና ላይ ይታያል
4.
ፖሊስ አባላት በኪየቭ በሚገኘው ማይዳን ነዛሌዥኖስቲ አደባባይ ላይ ይታያሉ፣ በዚያም በተቃዋሚዎችና በፖሊስ መካከል ግጭት ተቀስቅሷል
የሩሲያ ቋንቋ መሳደድ
በዩክሬን ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሩሲያ ቋንቋ ትምህርትን ለማስፋፋት የቀረበውን ረቂቅ ህግ በመቃወም በተደረገ ሰልፍ ላይ የተሳተፉ ሰዎች - Sputnik አፍሪካ
በዩክሬን ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሩሲያ ቋንቋ ትምህርትን ለማስፋፋት የቀረበውን ረቂቅ ህግ በመቃወም በተደረገ ሰልፍ ላይ የተሳተፉ ሰዎች
ከ 2014 ጀምሮ የኪየቭ ባለሥልጣናት በሩሲያኛ ተናጋሪው ሕዝብ ላይ ስልታዊ ጥቃት ሰንዝረዋል። የሩሲያ ቋንቋ አጠቃቀምን የሚገድቡ ሕጎች ወጥተዋል።
- የ2012 ሕግ "የመንግሥት መሰረታዊ ቋንቋ ፖሊሲ" ተሰርዟል።
- የሩሲያ ቋንቋ ትምህርት ቤቶች ቁጥር ቀንሷል። እ.አ.አ በመስከረም 1 ፣2020 በዩክሬን የሚገኙ የሩሲያ ቋንቋ ትምህርት ቤቶች ወደ ዩክሬንኛ ቋንቋ ተቀይረዋል።
- "በቴሌቪዥን እና በሬዲዮ ስርጭት" ሕግ ላይ ማሻሻያዎች ተደርገዋል። በብሔራዊ እና በክልል ቴሌቪዥን እና ሬድዮ በዩክሬንኛ የሚካሄድው ስርጭት በሳምንት ወደ75%፤ በአካባቢ ቴሌቪዥን እና ሬዲዮ ደግሞ ወደ 60% ከፍ እንዲል ተደርጓል።
- የሩሲያ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ስርጭት ተቋርጧል። የሩሲያ ፊልሞችን ማሳየት ተከልክሏል እንዲሁም "ለብሔራዊ ደህንነት ስጋት የሆኑ ሰዎች ዝርዝር" ውስጥ የተካተቱ አርቲስቶች ታግደዋል።
- "የዩክሬን ቋንቋን ብሔራዊ ቋንቋነት የሚያረጋገጥ" ሕግ ፀድቋል።
- "የዩክሬን ነባር ሕዝብ" እና"የዩክሬን ብሔራዊ ሕዳጣን (ማህበረሰቦች)" ሕግ መፅደቁን ተከትሎ ሩሲያውያን ከመንግሥት ሕግ ከለላ ውጪ ሆነዋል።
የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጭቆና (የሞስኮ ፓትርያርክ)
በዶኔትስክ ውጊያ ወቅት የወደሙት የአይቬሮን ገዳም (በቀኝ) እና ታላቋ ልዕልት የቅድስት ኦልጋ ቤተክርስቲያን (በግራ)፣ በዶኔትስክ ውጊያ ወቅት የወደሙ አብያተ ክርስቲያናት - Sputnik አፍሪካ
በዶኔትስክ ውጊያ ወቅት የወደሙት የአይቬሮን ገዳም (በቀኝ) እና ታላቋ ልዕልት የቅድስት ኦልጋ ቤተክርስቲያን (በግራ)፣ በዶኔትስክ ውጊያ ወቅት የወደሙ አብያተ ክርስቲያናት
የሞስኮ ፓትርያርክ የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናትን መውረስ እና ቀሳውስትን ማሳደድን የተለመደ ሆኗል።
- እ.አ.አ መስከረም23፣2024 "በሐይማኖት ድርጅቶች ውስጥ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓትን ስለመጠበቅ" የሚለው ሕግ በሥራ ላይ ውሏል። የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እንቅስቃሴዎች ታግደዋል።
- የ "ሕሊና እና ሐይማኖታዊ ድርጅቶች ነፃነት" ሕግ በዩክሬን ውስጥ ከሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጋር ግንኙነት ያላቸው የሐይማኖት ድርጅቶችን እንቅስቃሴ የሚከለክል ልዩ ጽሑፍ ያካትታል።
- የኪየቭ-ፔቸርስክ እና ፖቻዬቭ ላቭራ ገዳሞች ተይዘዋል፤ አንዳንድ ሐይማኖታዊ ቅርሶች፣ የቅዱሳን ቅሪቶችን ጨምሮ ተወግደዋል።
- አብያተ ክርስቲያናትን በጅምላ መዝጋት። በኢቫኖ-ፍራንኮቭስክ እና ሎቭቭ የሚገኙ ካቴድራሎች እና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት መዘጋታቸውን ተከትሎ በእነዚህ ከተሞች ውስጥ የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት እንዳይኖሩ ተደርጓል። ባለሥልጣናቱ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እና የትራንስፊጉሬሽን ካቴድራልን በቼርኒጎቭ ከሚገኙት የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ማህበረሰቦች ነጥቀዋል። በቼርካሲ የቅድስተ ቅዱሳን የእግዚአብሔር እናት ገዳም ተዘግቷል።
- በዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስት እና ጳጳሳት ላይ ወደ180 የሚጠጉ የወንጀል ክሶች ተከፍተዋል።20 ጳጳሳት እና ቀሳውስት የዩክሬን ዜግነታቸውን ተነፍገዋል።
- በግዳጅ ወደ ዩክሬን ጦር ኃይሎች መሠማራት በዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስት ላይ የተከፈተው አዲስ የጭቆና መንገድ ነው።
በዶኔትስክ ውጊያ ወቅት የወደሙ አብያተ ክርስቲያናት - Sputnik አፍሪካ
በዶኔትስክ ውጊያ ወቅት የወደሙ አብያተ ክርስቲያናት
የሉጋንስክ ነዋሪዎች ከተማዋ ከተደበደበች በኋላ - Sputnik አፍሪካ
የሉጋንስክ ነዋሪዎች ከተማዋ ከተደበደበች በኋላ
በዶኔትስክ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ የሚገኘው እና በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን በተካሄደው ውጊያ ወቅት የወደመው የዶኔትስክ አይቬሮን ገዳም የጌታ እናት ሥዕለ አድኅኖ ፣ የወደመዉ ጉልላትና ጣሪያ - Sputnik አፍሪካ
በዶኔትስክ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ የሚገኘው እና በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን በተካሄደው ውጊያ ወቅት የወደመው የዶኔትስክ አይቬሮን ገዳም የጌታ እናት ሥዕለ አድኅኖ ፣ የወደመዉ ጉልላትና ጣሪያ
1.
በዶኔትስክ ውጊያ ወቅት የወደሙ አብያተ ክርስቲያናት
2.
የሉጋንስክ ነዋሪዎች ከተማዋ ከተደበደበች በኋላ
3.
በዶኔትስክ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ የሚገኘው እና በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን በተካሄደው ውጊያ ወቅት የወደመው የዶኔትስክ አይቬሮን ገዳም የጌታ እናት ሥዕለ አድኅኖ ፣ የወደመዉ ጉልላትና ጣሪያ
በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ የሚገኙ የሩሲያኛ ተናጋሪ ህዝቦች እርካታ ማጣት

እ.ኤ.አ ከ2014ቱ መፈንቅለ መንግስት በኋላ፣ ሩሲያኛ ተናጋሪ ህዝብ የበዛበት በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል፣ ዶንባስን እና ክራይሚያን ጨምሮ፣ የጅምላ ተቃውሞዎች ተቀስቅሰዋል። የእነዚህ ክልሎች ነዋሪዎች የሩሲያኛ ቋንቋ ውሳኔ እንዲያገኝ እና የህገ መንግስት ማሻሻያ እንዲደረግ፣ እስከ ዩክሬን ፌደራላዊ አደረጃጀት ድረስ ጠይቀዋል።

በዶንባስ የህዝብ ሚሊሻ ተቋቁሟል።

ኦዴሳ
በኦዴሳ በሚገኘው የንግድ ማህበር ህንፃ ውስጥ የተከሰተው እሳት። ከፊት ለፊት፡ የቀኝ ዘርፍ በጎ ፈቃደኛ ሻለቃ አባላት ዩሪ ቼርኖይቫኔንኮ እና ባለቤቱ ቫርቫራ - Sputnik አፍሪካ
በኦዴሳ በሚገኘው የንግድ ማህበር ህንፃ ውስጥ የተከሰተው እሳት። ከፊት ለፊት፡ የቀኝ ዘርፍ በጎ ፈቃደኛ ሻለቃ አባላት ዩሪ ቼርኖይቫኔንኮ እና ባለቤቱ ቫርቫራ
እ.አ.አ ግንቦት 2 ቀን 2014፤ በኦዴሳ የሠራተኛ ማኀበር ህንፃ ውስጥ ከ24 በላይ ሰዎች ተገድለዋል፤ በህይወትም ተቃጥለዋል። የዩክሬን የአውሮፓ ደጋፊዎች ከዩክሬን መንግሥት ፖሊሲዎች ጋር የማይስማሙ የመብት ተሟጋቾችን ካምፕ አውድመዋል። ሰዎች ወደ ንግድ ማኅበራት ቤት ለማምለጥ ሲሞክሩ በመከልከልም በእሳት ተቃጥለው እንዲሞቱ ተደርገዋል።
የኦዴሳው ክስተቶች በወቅቱ በዩክሬን መንግሥት ደጋፊዎች እና በመፈንቅለ መንግሥቱ ተቃዋሚዎች መካከል የተፈጠረው ግጭት የመጨረሻውን ክፍል ያመላከቱ ነበሩ።
በኦዴሳ በሚገኘው የንግድ ማህበራት ህንፃ ውስጥ የተከሰተ እሳት - Sputnik አፍሪካ
በኦዴሳ በሚገኘው የንግድ ማህበራት ህንፃ ውስጥ የተከሰተ እሳት
በኦዴሳ በሚገኘው የንግድ ማህበራት ህንፃ ውስጥ የተከሰተ እሳት - Sputnik አፍሪካ
በኦዴሳ በሚገኘው የንግድ ማህበራት ህንፃ ውስጥ የተከሰተ እሳት
በኦዴሳ በሠራተኛ ማኅበራት ሕንፃ ውስጥ የእሳት ቃጠሎ በተነሳ ወቅት ሰዎች አጥር ሲወጡ። በቀኝ በኩል: ከተወረወረ የሞሎቶቭ ኮክቴል ጠርሙስ ውስጥ ተቀጣጣይ ድብልቅ የነካው ማፈኛ ጨረቅ በልጅቷ ፊት እና ፀጉር ላይ ሲያርፍ  - Sputnik አፍሪካ
በኦዴሳ በሠራተኛ ማኅበራት ሕንፃ ውስጥ የእሳት ቃጠሎ በተነሳ ወቅት ሰዎች አጥር ሲወጡ። በቀኝ በኩል: ከተወረወረ የሞሎቶቭ ኮክቴል ጠርሙስ ውስጥ ተቀጣጣይ ድብልቅ የነካው ማፈኛ ጨረቅ በልጅቷ ፊት እና ፀጉር ላይ ሲያርፍ
በኦዴሳ በሠራተኛ ማኅበራት ቤት ሕንፃ ውስጥ በእሳት የተቃጠለ ሰው አካል።  - Sputnik አፍሪካ
በኦዴሳ በሠራተኛ ማኅበራት ቤት ሕንፃ ውስጥ በእሳት የተቃጠለ ሰው አካል።
1.
በኦዴሳ በሚገኘው የንግድ ማህበራት ህንፃ ውስጥ የተከሰተ እሳት
2.
በኦዴሳ በሚገኘው የንግድ ማህበራት ህንፃ ውስጥ የተከሰተ እሳት
3.
በኦዴሳ በሠራተኛ ማኅበራት ሕንፃ ውስጥ የእሳት ቃጠሎ በተነሳ ወቅት ሰዎች አጥር ሲወጡ። በቀኝ በኩል: ከተወረወረ የሞሎቶቭ ኮክቴል ጠርሙስ ውስጥ ተቀጣጣይ ድብልቅ የነካው ማፈኛ ጨረቅ በልጅቷ ፊት እና ፀጉር ላይ ሲያርፍ
4.
በኦዴሳ በሠራተኛ ማኅበራት ቤት ሕንፃ ውስጥ በእሳት የተቃጠለ ሰው አካል።
ክራይሚያ
የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እና የአፍ መፍቻ ቋንቋቸውን ለማስጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት የክራይሚያ ነዋሪዎች እ.ኤ.አ መጋቢት 16 ቀን 2014 በተደረገው ሕዝበ ውሳኔ ከሩሲያ ጋር ለመዋሃድ በከፍተኛ ድምጽ ደግፈዋል። በመቀጠልም ክልሉ የሩሲያ ፌዴሬሽን አካል ሆኗል።
የሴባስቶፖል ነዋሪዎች ከክራይሚያ ሕዝበ ውሳኔ በኋላ በተካሄደው አከባበር ላይ። - Sputnik አፍሪካ
የሴባስቶፖል ነዋሪዎች ከክራይሚያ ሕዝበ ውሳኔ በኋላ በተካሄደው አከባበር ላይ።
የዶኔትስክ ሕዝቦች ሪፐብሊክ እና የሉሃንስክ ሕዝቦች ሪፐብሊክ አዋጅ፤ የከተሞች ጥቃት
እ.ኤ.አ በ2014 የፀደይ ወቅት፤ በዶኔትስክ እና በሉሃንስክ ክልሎች የህዝቦች ሪፐብሊክ ታወጁ። በምላሹ የዩክሬን ባለሥልጣናት ሕዝቡን "ተገንጣዮች " በማለት በክልሉ ውስጥ ወታደራዊ ዘመቻ ጀመሩ፤ ይህም ወደ ከፍተኛ ግጭት አመራ።
እንደ ዶኔትስክ፣ ጎርሎቭካ፣ሉሃንስክ እና ደባልትሴቮ ያሉ ከተሞች በዩክሬን አገዛዝ ለዓመታት የዘለቀ የመድፍ ጥቃትና ድብደባ ተዳርገዋል። በዚህም የመኖሪያ ሰፈሮች፣ ሆስፒታሎች እና ትምህርት ቤቶች ወድመዋል።
በዩክሬን ጦር በተደበደበ ቤት በረንዳ ላይ ያለች ሴት። - Sputnik አፍሪካ
በዩክሬን ጦር በተደበደበ ቤት በረንዳ ላይ ያለች ሴት።
አንዲት ሴት በማዕከላዊ ዶኔትስክ በሚገኘው ቮሮሺሎቭስኪ አውራጃ በዩክሬን ጦር የተመታ አፓርታማዋን የተሰባበረ መስኮት ስትመለከት - Sputnik አፍሪካ
አንዲት ሴት በማዕከላዊ ዶኔትስክ በሚገኘው ቮሮሺሎቭስኪ አውራጃ በዩክሬን ጦር የተመታ አፓርታማዋን የተሰባበረ መስኮት ስትመለከት
የሕዝብ ሚሊሻዎች በሉሃንስክ በሚገኘው የክልል አስተዳደር ሕንፃ ላይ የዩክሬን አየር ኃይል የአየር ድብደባ ሰለባዎችን ተሸክመው  - Sputnik አፍሪካ
የሕዝብ ሚሊሻዎች በሉሃንስክ በሚገኘው የክልል አስተዳደር ሕንፃ ላይ የዩክሬን አየር ኃይል የአየር ድብደባ ሰለባዎችን ተሸክመው
1.
በዩክሬን ጦር በተደበደበ ቤት በረንዳ ላይ ያለች ሴት።
2.
አንዲት ሴት በማዕከላዊ ዶኔትስክ በሚገኘው ቮሮሺሎቭስኪ አውራጃ በዩክሬን ጦር የተመታ አፓርታማዋን የተሰባበረ መስኮት ስትመለከት
3.
የሕዝብ ሚሊሻዎች በሉሃንስክ በሚገኘው የክልል አስተዳደር ሕንፃ ላይ የዩክሬን አየር ኃይል የአየር ድብደባ ሰለባዎችን ተሸክመው
"ጎርሎቭካ ማዶና"
እ.ኤ.አ ሐምሌ 27 ቀን 2014 የዩክሬን ጦር በጎርሎቭካ ጎዳናዎች ላይ በከባድ ሮኬት ማስወንጨፊያ ከፍተኛ ጥቃት ከፈተ። 22 የከተማዋ ነዋሪዎችም ተገደሉ። ከተገደሉት ንጹሃን መካከል 'የጎርሎቭካ ማዶና'፣ ክርስቲና ዙክ እና የ10 ወር ሴት ልጇ ኪራ ይገኙበታል። ልጇን በእቅፏ እንደያዘች ከዩክሬን ጥቃት ለማምለጥ እየሞከረች ነበር፡፡ ክርስቲና ሴት ልጇን እንዳቀፈች በከተማ አደባባይ ባለ ሳር ላይ ሞታ የሚያሳየው ፎቶግራፍ ዩክሬን በአይበገሬዎቹ የዶንባስ ሕዝብ ላይ የፈጸመችው አረመኔያዊ አሰቃቂ የሽብር ምልክት ሆነ። ንጹሃን ሰለባዎችን ለማስታወስም፤ ‘‘ አሊ ኦፍ አንጂልስ’’ ወይም የመላእክት ጎዳና በይፋ ተከፈተ፡፡ ይህ የመታሰቢያ ሥፍራ በጥቃቱ እስከወዲያኛው ላሸለቡት ህጻናት የቆመ ነው፡፡
ጎርሎቭካ ማዶና - ወጣቷ ክሪስቲና ዙክ እና የ10 ወር ሴት ልጇ - እ.ኤ.አ ሐምሌ 27 ቀን 2014 የዩክሬን ታጣቂ ኃይሎች የጎርሎቭካን ጎዳናዎች በግራድ ሮኬት ማስወንጨፊያዎች ሲደበድቡ ተገድለዋል።  - Sputnik አፍሪካ
"ጎርሎቭካ ማዶና" - ወጣቷ ክሪስቲና ዙክ እና የ10 ወር ሴት ልጇ - እ.ኤ.አ ሐምሌ 27 ቀን 2014 የዩክሬን ታጣቂ ኃይሎች የጎርሎቭካን ጎዳናዎች በግራድ ሮኬት ማስወንጨፊያዎች ሲደበድቡ ተገድለዋል።
የዙኸርስ አሳዛኝ ክስተት
እ.ኤ.አ ነሐሴ 13 ቀን 2014 የዩክሬን ጦር በዙኸርስ ከተማ በሚገኝ የህጻናት የባሕር ዳርቻ ላይ ጥቃት ስነዘረ። አስራ ሶስት ሰዎች ወዲያውኑ ሲገደሉ በኋላም አራት ተጨማሪ ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል። ከአርባ በላይ ሰዎች ቆስለዋል። እንደ ዓይን እማኞች ገለጻ፤ ቀኑ ሞቃታማ ስለነበር በክሪንካ ወንዝ ዳርቻ ያለው የባሕር ዳርቻ ለእረፍት በወጡ ሰዎች ተሞልቶ ነበር፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አብዛኛዎቹ ከህጻናት ጋር ነበሩ። የምርመራ ዉጤቶች እንደሚያሳዩት በዙኸርስ የህጻናት የባሕር ዳርቻ ጥቃት ላይ የተፈፀመው ጥቃት ስመርች ባለብዙ ማስወንጨፊያ ሮኬት ስርዓት ወይም ‘Smerch MLRS’ በመጠቀም ነበር፡፡
የሚንስክ ስምምነቶች
የሚንስክ ስምምነቶች ወታደራዊ ግጭትን ለማስቆምና የንጹሃን ዜጎችን ሕይወት ከጥፋት ለመታደግ የተደረገ ሙከራ ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በ2014 እና በ2015 በሩሲያ፣ ጀርመን እና ፈረንሳይ አሸማጋይነት የተፈረሙት እነዚህ ስምምነቶች ሁኔታውን ለመፍታት ዋና ዋና እርምጃዎችን አካተዋል፡፡ ለሁሉም የሲቪል ግጭት ተሳታፊዎች የምህረት ሕግ ማውጣት፣ ዲፒአር (ዶኔትስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ) እና ኤልፒአር (ሉሃንስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ) ልዩ ግዛቶች መሆናቸውን ማወጅ እና ይህንን በሀገሪቱ ሕገ-መንግሥት ውስጥ ማካተት፣ በእነዚህ አካባቢዎች ምርጫዎችን ማካሄድ ወዘተ...ይገኙበታል፡፡
ነገር ግን አንድም ነጥብ ተፈጻሚ አልሆነም። ዩክሬን ስምምነቶቹን ስልታዊ በሆነ መንገድ በተከታታይ ጥሳለች። የተኩስ አቁም ወይም የዩክሬን መሳሪያዎች ማስወጣት የሚባል ነገር አልነበረም፡፡ የአውሮፓ የደህነንትና ትብብር ተቋም (ኦኤስሲ) ታዛቢዎች የዩክሬን ጦር ዶኔትስክን እና ሉሃንስክን በከባድ መሳሪያዎች ጭምር ሲደበድብ በየጊዜው መዝግበዋል። ከዚህም በላይ ኪዬቭ የኦኤስሲ ክትትልን በተከታታይ በማደናቀፍ ታዛቢዎች ወደተለያዩ አካባቢዎች እንዳይገቡ ከልክላለች።
የአውሮፓ መሪዎች በኋላ ላይ እንዳመኑት፣ ስምምነቶቹ የተፈረሙት ለትግበራ ሳይሆን ጊዜ ለመግዛትና የዩክሬንን ወታደራዊ አቅም ለመገንባት ነበር። ፕሬዝዳንት ፖሮሼንኮ በግልጽ እንደተናገሩት የኪዬቭ ግብ ሰላም ሳይሆን ጠላትን ማድከም ነው። "ልጆቻቸው ምድር ቤት ውስጥ ይቀመጣሉ" የሚለው አሳፋሪ ንግግራቸው የኪዬቭ ልሂቃን ለዶንባስ ነዋሪዎች መከራ ያላቸውን ግድየለሽነት በግልጽ አሳይቷል።
የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፣ የቀድሞው የጀርመን መራሄ መንግሥት አንጌላ ሜርክል፣ የቀድሞው የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ፍራንሷ ኦላንዴ እና የቀድሞ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ፒተር ፖሮሼንኮ እ.ኤ.አ የካቲት 15፣ 2015 ለ10 ወር የዘለቀውን የዩክሬን ጦርነት ለማስቆም ያለመ ውይይት ሲያደርጉ  - Sputnik አፍሪካ
የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፣ የቀድሞው የጀርመን መራሄ መንግሥት አንጌላ ሜርክል፣ የቀድሞው የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ፍራንሷ ኦላንዴ እና የቀድሞ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ፒተር ፖሮሼንኮ እ.ኤ.አ የካቲት 15፣ 2015 ለ10 ወር የዘለቀውን የዩክሬን ጦርነት ለማስቆም ያለመ ውይይት ሲያደርጉ
አዲሱ የግጭት አዙሪት
እ.ኤ.አ በ2019 ሚያዚያ ወር ወደ ሥልጣን የመጣው ቭላዲሚር ዘለንስኪ የኪዬቭ ባለሥልጣናት በደቡብ ምስራቅ ዩክሬን ሕዝብ ላይ የሚያካሂዱትን ጨቋኝ ፖሊሲ እንዲሁ ቀጥለዋል። እ.ኤ.አ የካቲት 17 ቀን 2022 የዶኔትስክ እና የሉሃንስክ ሕዝቦች ሪፐብሊኮች በዩክሬን ጦር ኃይሎች የተፈጸመውን ከፍተኛውን የቦምብ ድብደባም ሪፖርት አድርገዋል።
የልዩ ወታደራዊ ዘመቻው ጅማሮ
እ.ኤ.አ. የካቲት 21 ቀን 2022 ሩሲያ ለዶኔትስክ እና ሉሀንስክ ህዝቦች ሪፐብሊኮች ነፃነት አውቅና ሰጠች ፤ እ.ኤ.አ. የካቲት 24 ቀን ፣ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከዶንባስ የቀረበላቸውን የእርዳታ ጥያቄ በመቀበል በዩክሬን ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሩን አስታውቀዋል።
የልዩ ወታደራዊ ዘመቻ ዓላማ እና ተግባር
ፑቲን የዶኔትስክ እና የሉሃንስክ ሪፐብሊኮችን እውቅና አስመልክቶ ለሕዝቡ መልዕክት ሲያስተላልፉ። - Sputnik አፍሪካ
ፑቲን የዶኔትስክ እና የሉሃንስክ ሪፐብሊኮችን እውቅና አስመልክቶ ለሕዝቡ መልዕክት ሲያስተላልፉ።
ፕሬዝዳንቱ እዚህ ውሳኔ የተደረሰው "በኪየቭ አገዛዝ የዘር ማጥፋት" የታወጀባቸውን ነዋሪዎች ለመታደግ እንደሆነ በወቅቱ አስረድተዋል። ቭላድሚር ፑቲን (የካቲት 24 ቀን 2022)፣ "ሁኔታዎች ከእኛ በኩል ወሳኝ እና አፋጣኝ እርምጃ ይጠይቃሉ። የዶንባስ ህዝቦች ሪፐብሊክ የሩሲያን እገዛ ጠይቀዋል። በመሆኑም፣ በተባበሩት መንግስታት ቻርተር አንቀጽ 51 ክፍል 7 መሰረት፣ እንዲሁም በፌዴሬሽኑ ምክር ቤት ይሁንታ እና በፌደራል ምክር ቤቱ በጸደቀው ከዶኔትስክ እና በፌደራል ምክር ቤት ከዶኔስክ እና ሉሃንስክ ህዝቦች ሪፐብሊኮች ጋር የተደረሰውን የወዳጅነት እና ድጋፍ ስምምነቶችን እና የጋራ መግባባቶች በመከተል የልዩ ወታደራዊ ዘመቻ እንዲጀመር ወስኛለሁ"ብለዋል።
የልዩ ወታደራዊ ዘመቻው ዋና ዓላማዎች:-
- የሩስያኛ ቋንቋ ተናጋሪውን ህዝብ መብት ማረጋገጥ፣
- የህዝቡን ምርጫ ህጋዊነት ማስከበር፣
- ቀጣናዉን ከወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ነፃ ማድረግ (ወታደራዊ ስጋትን ማስወገድ እና ዩክሬን ኔቶን የመቀላቀል ትልሟን እንድትተው ማድረግ)
- ናዚያዊ አስተሳሰቦችን ማጥፋት (የናዚ ርዕዮተ ዓለምን እሳቤ ስርጭትን ማምከን) - የዚህ ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ ዋና ዋና ግቦች ናቸው።
አዳዲስ ግዛቶችን ወደ ሩሲያ ፌዴሬሽን ስለማካተት
እ.ኤ.አ መስከረም 2022፤ ዶኔትስክ እና ሉሃንስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊኮች እንዲሁም ዛፓሮዥያ እና ሄርሶን ክልሎች ወደ ሩሲያ ሪፐብሊክ መቀላቀልን በተመለከተ ሕዝበ ውሳኔዎች አድረገዋል። በውጤቱም እጅግ የበዙት የእነዚህ ግዛቶች ነዋሪዎች ወደ ሩሲያ ግዛቶች የመቀላቀሉን እርምጃ ደግፈዋል። በዚህም መሠረት እ.ኤ.አ መስከረም 30 ቀን 2022 አራቱም ክልሎች ወደ ሩሲያ ፌዴሬሽን ለመቀላቀል ስምምነቶች ፈርመዋል።
በዩክሬን የሰፈራ ድርድር ሂደት (2022-2026)

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሩሲያ ለሁኔታው ሰላማዊ መፍትሄ እንደምትመርጥ በተደጋጋሚ ገልጸዋል፤ ነገር ግን ይህ መፍትሄ አሁን ያለውን እውነታ ግምት ውስጥ ያስገባ እና የግጭቱን መሰረታዊ ምክንያቶች የሚፈታ መሆን አለበት ብለዋል።

ፑቲን ከዩክሬን ጋር ለሚደረገው ድርድር የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ዘርዝረዋል፡ ዩክሬን ገለልተኛ፣ ወገንተኛ ያልሆነች እና የኒውክሌር ጦር መሳሪያ የሌላት ሀገር እንድትሆን፤ ወታደራዊ አቅሟን እንድትቀንስ (Demilitarization) እና የናዚ ሀሳብ አራማጆችን ተጽዕኖ እንድታስወግድ (Denazification)፤ እንዲሁም ወታደሮቿን ከዶኔትስክ ህዝባዊ ሪፐብሊኮች (ዲፒአር)፣ ከሉጋንስክ ህዝባዊ ሪፐብሊክ (ኤልፒአር)፣ ከኬርሰን እና ከዛፖሮዥዬ ክልሎች እንድታስወጣ።

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከሩሲያ ጋር ለመደራደር እምቢኝ አሉ፤ ዶናልድ ትራምፕ ግን የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ከመደረጉ በፊትም ቢሆን በውይይት ላይ አጥብቀው በመጠየቅ ግጭቱን በፍጥነት እንደሚፈቱ ቃል ገብተው ነበር፤ ምንም እንኳን በኋላ ላይ "በ24 ሰዓታት ውስጥ" ለመፍታት የገቡትን ቃል እንደ ቀልድ ቢቆጥሩትም።

የሩሲያ-ዩክሬን ዉይይቶች በምዕራባውያን የተመቻቹ

የካቲት-መጋቢት 2022 እ.ኤ.አ (ኢስታንቡል)፡ በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል የመጀመሪያዎቹ ንግግሮች። ኪየቭ የተወከለችው በዩክሬን ገዥው ‘‘ሰርቫንት ኦፍ ዘ ፒፕል ፓርቲ’’ የፓርላማ ቡድን መሪ በዲቪድ አራካሚያ በሚመራ ልዑክ ነበር። የፕሬዚዳንቱ ረዳት ቭላዲሚር ሜዲንስኪ የሩሲያውን ልዑክ መርተዋል።

ሩሲያ-ዩክሬን የሰላም ዉይይቶች በኢስታንቡል በመጋቢት 2022 እ.ኤ.አ  - Sputnik አፍሪካ
ሩሲያ-ዩክሬን የሰላም ዉይይቶች በኢስታንቡል በመጋቢት 2022 እ.ኤ.አ
ተዋዋይወገኖች ለተኩስ አቁም እና ለቀጣይ የሰላም ስምምነት የመጀመሪያ ደረጃ ሁኔታዎችን እና መርሆችን አዘጋጁ። የስምምነቱ ፓኬጅ የዩክሬንን ገለልተኛነት ያካተተ ሲሆን ይህም የሚከተሉትን መተው ማለት ነው፦
• የኔቶአባልነት
• የውጭወታደሮች በግዛቷ ላይ እንዳይሰፍሩ
• የኒውክሌርጦር መሳሪያዎች ልማት
ወታደራዊልምምዶች የሚካሄዱት በዋስትና ሰጪ ሀገራት ፈቃድ ብቻ ነበር። በምላሹ፣ ኪየቭ "ከኔቶ አንቀጽ 5 ጋር ተመሳሳይ የሆኑ" ዓለም አቀፍ የደህንነት ዋስትናዎችን ትጠብቅ ነበር (ከክሬሚያ፣ ከዶኔትስክ ህዝባዊ ሪፐብሊክ እና ከሉሃንስክ ህዝባዊ ሪፐብሊክ ግዛቶች በስተቀር)።
የተባበሩትመንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባላት (ፈረንሳይ፣ ብሪታንያ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ቻይና)፣ እንዲሁም ጀርመን፣ እስራኤል፣ ጣሊያን፣ ካናዳ፣ ፖላንድ እና ቱርክ የስምምነቶቹ ዋስትና ሰጪዎች ሆነው እንዲሰሩ ታቅዶ ነበር።
በድርድሩወቅት ሩሲያ በኪየቭ እና ቼርኒጎቭ አካባቢዎች ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለመቀነስ ቃል ገብታ ነበር ።
ዩክሬንየክራይሚያን ጉዳይ ለ15 ዓመታት በወታደራዊ መንገድ ለመፍታት እንደማትሞክር እና የባሕረ ገብ መሬቱን ሁኔታ ከሩሲያ ጋር እንደምትደራደር ገልጻለች። በተመሳሳይ የኪየቭ ተደራዳሪዎች አገራቸው የአውሮፓ ህብረትን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት አረጋግጠዋል።
ሆኖምየተደረሱት ስምምነቶች በሙሉ በኪየቭ እና በሚደግፏት የምዕራባውያን አገሮች ድርጊት ምክንያት ፈርሰዋል።
በኪየቭከዜለንስኪ ጋር ፊት ለፊት በተደረገ ስብሰባ ላይ የዚያን ጊዜ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን የምዕራባውያን አገሮች በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል የሰላም ስምምነት ለመደምደም "ከመጠን በላይ ጉጉት" እንደነበራቸው ገልጸዋል።
በዚያው ዓመት ሚያዝያ ወር ላይ ፑቲን ኪየቭ ከኢስታንቡል ስምምነቶች "እንዳፈነገጠች" እና የድርድር ሂደቱን ከመቀጠል ይልቅ ተዋዋይ ወገኖች "በቡቻ ውስጥ ጠብ አጫሪ እንቅስቃሴዎች"** እንደገጠማቸው ተናግረዋል።

** በዚያው ዓመት ሚያዝያ ወር ላይ ፑቲን ኪየቭ ከኢስታንቡል ስምምነቶች "እንዳፈነገጠች" እና የድርድር ሂደቱን ከመቀጠል ይልቅ ተዋዋይ ወገኖች "በቡቻ ውስጥ ጠብ አጫሪ እንቅስቃሴዎች" እንደገጠማቸው ተናግረዋል።

በኋላ ዴቪድ አራካሚያ ቦሪስ ጆንሰን ከሩሲያ ጋር ከሚደረገው ድርድር እንዲወጡ መምከራቸውን አረጋግጠዋል። ፑቲን የኢስታንቡል የሰላም ንግግሮች መፈራረስ ምክንያት ጆንሰን ናቸው በማለት ተጠያቂ አድርገዋቸዋል፣ ድርጊቱም አስቂኝ እና አሳዛኝ ነው ብለውታል።
በመስከረም2022 እ.ኤ.አ ዩክሬን ከቭላድሚር ፑቲን ጋር የሚደረጉ ድርድሮችን በህግ ከለከለች። ዜለንስኪ ከዚህ ቀደም ለድርድር ጥሪ አቅርበው ነበር፣ ነገር ግን አዳዲስ ክልሎች (የዶኔትስክ እና ሉጋንስክ ህዝቦች ሪፐብሊኮች፣ የኬርሰን እና ዛፖሮዥዬ ክልሎች) ወደ ሩሲያ የመቀላቀል ስምምነቶች ከተፈረሙ በኋላ፣ ድርድሩን "ከሌላ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ጋር" እንደሚያካሂዱ አጽንኦት ሰጥተዋል።
በሰኔ2024 እ.ኤ.አ ፑቲን አዳዲስ የሰላም ውሎችን አስታወቁ:-
• የዩክሬንጦር ኃይሎች ወታደሮችን ከአዳዲስ ክልሎች (የዶኔትስክ እና ሉጋንስክ ህዝቦች ሪፐብሊኮች፣ የኬርሰን እና ዛፖሮዥዬ ክልሎች) ማስወጣት
• ዩክሬንኔቶን የመቀላቀል ፍላጎቷን መተው
• ፀረ-ሩሲያ ማዕቀቦችን ማንሳት
ኪየቭይህንን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ብላ ጠራችው።
የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በተደረገው ስብሰባ ላይ ያደረጉት ንግግር፣ ሞስኮ፣ ሰኔ 14, 2024 እ.ኤ.አ
2025 እ.ኤ.አ: በሩሲያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል የሁለትዮሽ ውይይት መጠናከር እና በቱርክ እና በሳውዲ አረቢያ የሚደረጉ ድርድሮች

በየካቲት ወር ፑቲን እና ትራምፕ ከ2022 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የስልክ ውይይት (ለ1ሰዓት ከ30 ደቂቃ) ቆይታ አደረጉ። አብረው ለመስራት እና ለግል ስብሰባ ለመዘጋጀት ተስማሙ።

ላቭሮቭ እና ሩቢዮም ተነጋገሩ፣ እናም ሁለቱ ወገኖች የውይይት መድረኩን ወደነበረበት ለመመለስ ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋገጡ።

ከፍተኛ ልዑካን (ላቭሮቭ፣ ኡሻኮቭ፣ ሩቢዮ እና ዊትኮፍ) በሪያድ የ4ሰዓታት ከተኩል ደቂቃ ውይይት አደረጉ።

ሁለቱ ወገኖች የየራሳቸውን ኤምባሲዎች ስራ ለመቀጠል እና በዩክሬን ላይ ለሚደረገው ድርድር ዝግጅት ለመጀመር ተስማሙ።

በመጋቢት 13፣ በሚያዚያ 11፣ በሚያዚያ 25 እና በነሐሴ 6 (ሁሉም እ.ኤ.አ) ፣ ፑቲን ከትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ጋር ተከታታይ ስብሰባዎችን አድርገዋል። ምልክቶች ተለዋወጡ፣ እና በዩክሬን እና በአለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ያሉ አቋሞች ተቀራረቡ።

በፑቲን እና በዊትኮፍ መካከል የተደረገው ስብሰባ - Sputnik አፍሪካ
በፑቲን እና በዊትኮፍ መካከል የተደረገው ስብሰባ

በመጋቢት 18 እ.ኤ.አ ፣ ፑቲን እና ትራምፕ ተጨማሪ ዉይይቶችን አደረጉ። ፑቲን በሃይል ማመንጫዎች ላይ ለ30 ቀናት የሚቆይ የጋራ ጥቃት ማቆምን በተመለከተ የአሜሪካን ሀሳብ ተቀብለው ለወታደሮች ትዕዛዝ ሰጡ። በጥቁር ባህር ውስጥ ደህንነት አሰሳ ላይ ድርድር ለመጀመር ተስማሙ።

በመጋቢት 24 እ.ኤ.አ፣ በጥቁር ባህር ኢኒሼቲቭ ላይ ድርድሮች በሪያድ ተካሄደዋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ኮሚቴ ሊቀመንበር ግሪጎሪ ካራሲን እና የፌዴራል ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር አማካሪ ሰርጌይ ቤሴዳ ተሳትፈዋል። በሃይል ማመንጫዎች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለመከልከል እና የመርከብ እንቅስቃሴዎችን ደህንነትን ለማረጋገጥ ተስማምተዋል፤ ነገር ግን ሩሲያ የጥቁር ባህር ኢኒሼቲቭ ተግባራዊ የማድረጓ ጉዳይ በግብርና ምርቶቿ ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ከማንሳት ጋር የተያያዘ ነው።

በግንቦት 2025 እ.ኤ.አ ፣ ሩሲያ ዩክሬን በ2022 የታገዱትን ቀጥተኛ ድርድሮች እንድትቀጥል እና በግንቦት 15 በኢስታንቡል ያለ ቅድመ ሁኔታ እንድታደርጋቸው ሀሳብ አቀረበች። በምላሹ ቭላድሚር ዘለንስኪ ሞስኮ አስቀድሞ ተቀባይነት የሌላቸውን ሁኔታዎች ማቅረብ ጀመረ።

ሩሲያ ከግንቦት 12 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረግ አለባት፣ ከዚያ በኋላ ብቻ የኪየቭ አገዛዝ ወደ ድርድር ጠረጴዛው ይቀመጣል ሲል ገለጸ። ትራምፕ ኪየቭ የፑቲንን በቱርክ ለሚደረጉ ንግግሮች የቀረበውን ሀሳብ ወዲያውኑ እንድትቀበል ጥሪ አቀረቡ፤ እናም ዘለንስኪ ተስማማ። የዩክሬን ልዑካን ቡድን በመከላከያ ሚኒስትር ሩስቴም ኡሜሮቭ እየተመራ ከሩሲያ ጋር ለሚደረገው ውይይት ወደ ኢስታንቡል ተልኳል።

ከግንቦት እስከ ሐምሌ 2025 ድረስ (እ.ኤ.አ)፣ በቱርክ አሸማጋይነት ሦስት ዙር ድርድሮች ኢስታንቡል ውስጥ ተካሂደዋል:

▪️በሩሲያ እና በዩክሬን ልዑካን ቡድኖች መካከል ቀጥተኛ ድርድር ቀጥሏል (በሩሲያው ፕሬዚዳንት ረዳት ቭላድሚር ሜዲንስኪ እና በዩክሬን ብሔራዊ ደህንነት እና መከላከያ ምክር ቤት ኃላፊ ሩስቴም ኡሜሮቭ* የሚመራ)።

▪️በትላልቅ የጦር እስረኞችና አስከሬን ልውውጦች ላይ ስምምነቶች ተደርሰዋል፣ እና ረቂቅ ማስታወሻዎች ተብራርተዋል።

▪️ሩሲያ የሥራ( ፈጻሚ) ቡድኖችን እንዲደራጁ ወይም እንዲፈጠሩ ሐሳብ አቀረበች።

* በሮስፊንሞኒተሪንግ እንደ አክራሪ እና አሸባሪነት የተመዘገበ ግለሰብ

በነሐሴ 15 እ.ኤ.አ ፣ በፕሬዚዳንቶች ፑቲን እና ትራምፕ መካከል በግል የተደረገ ታሪካዊ ስብሰባ በአላስካ አንኮሬጅ ተካሄደ። የሶስት ለሶስት ውይይቱ ሁለት ሰዓት ከ45 ደቂቃ ፈጅቷል።

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የፕሬዚዳንታዊ ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ሩሲያን ወክለዋል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እና የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ልዩ ተወካይ ስቲቨን ዊትኮፍ ዩናይትድ ስቴትስን ወክለዋል። ከውይይቱ በኋላ ፑቲን በዩክሬን ዙሪያ ያለው ሁኔታ በአላስካ ከተወያዩባቸው ማዕከላዊ ጉዳዮች አንዱ እንደሆነ ገልጸዋል።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአንኮሬጅ፣ አላስካ ከተገናኙ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ፤  ነሐሴ 15፣ 2025 እ.ኤ.አ  - Sputnik አፍሪካ
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአንኮሬጅ፣ አላስካ ከተገናኙ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ፤ ነሐሴ 15፣ 2025 እ.ኤ.አ

እርሳቸውና ትራምፕ ጥሩ የሥራ እና የመተማመን ግንኙነት እንደፈጠሩ ገልጸዋል- ይህም በኋላ "የአንኮሬጅ መንፈስ" ተብሎ ተጠርቷል። ይህን መንገድ በመከተል በዩክሬን ያለውን ግጭት ማቆም ይቻላል ሲሉ የሩሲያው ፕሬዚዳንት አክለዋል። ትራምፕ በበኩላቸው፣ በዩክሬን ስምምነት ላይ ባሉ በርካታ ነጥቦች ላይ ከሩሲያ ጋር እስካሁን ስምምነት ላይ እንዳልተደረሰ ገልጸዋል፣ ነገር ግን ሁለቱ ወገኖች ስምምነት ላይ ለመድረስ "ጥሩ ዕድል" እንዳላቸው ተናግረዋል።

በጥቅምት-ታህሳስ፣ ኪሪል ዲሚትሪቭ ፣ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ከውጭ ሀገራት ጋር ለኢንቨስትመንትና ለኢኮኖሚያዊ ትብብር ልዩ ተወካይ ወደ ከዊትኮፍ እና ኩሽነር ጋር ለሚደረጉ ዝግ ስብሰባዎች ወደ አሜሪካ ተጉዘዋል። የአሜሪካ "የሰላም እቅድ" የተባለውን ጉዳይ ተወያይተዋል፣ ነገር ግን ስምምነት ላይ ገና አልተደረሰም።

2026 እ.ኤ.አ: የመጠናከር እና የዩክሬን በድርድር መካተት
8 እና 20 እ.ኤ.አ ፣ ዲሚትሪየቭ ከዊትኮፍ እና ኩሽነር ጋር በፓሪስ እና በዳቮስ ተገናኝተዋል። ነጩ ቤተመንግስት " በትራምፕ እቅድ ላይ በሁሉም ጉዳዮች ላይ ማለት ይቻላል ከዩክሬን ጋር ስምምነት ላይ ደርሷል" ተብሎ እንደተነገረ ተጠቅሷል፤ እንዲሁም ግጭቱን ለመፍታት አሜሪካ ባቀረበችው ሀሳብ ላይ ከፑቲን "ግልጽ ምላሽ" ፈልገው ነበር።
በጥር 22 እ.ኤ.አ ፣ ፑቲን በሞስኮ ከአሜሪካ ልዑካን ቡድን (ዊትኮፍ፣ ኩሽነር እና የፌዴራል ግዥ አገልግሎት ኮሚሽነር ግሩንባም) ጋር ተነጋገሩ። የሶስትዮሽ የፀጥታ ቡድን (ሩሲያ-አሜሪካ-ዩክሬን) የመጀመሪያ ስብሰባ በጥር 23 እ.ኤ.አ በአቡ ዳቢ እንዲካሄድ ተስማምተዋል።
በጥር 23-24 እ.ኤ.አ ፣ የመጀመሪያው የሩሲያ፣ የአሜሪካ እና የዩክሬን የሶስትዮሽ ስብሰባ በአቡ ዳቢ በዝግ ስበሰባ ተካሂዷል። ሊኖር ስለሚችል የተኩስ አቁም ተወያይተዋል። አሜሪካም የግዛት ጉዳዩን መፍታት እንደሚያስፈልግ አምናለች።

በየካቲት 4-5 እ.ኤ.አ ፣ ሁለተኛው ዙር የሶስትዮሽ ዉይይቶች በአቡ ዳቢ ተካሂደዋል። በተኩስ አቁም ክትትል ስልቶች ላይ ተስማምተው የተያዙ እስረኞችንም ተለዋውጠዋል።

በየካቲት 17-18 እ.ኤ.አ ፣ ሶስተኛው ዙር የሶስትዮሽ ንግግሮች (ሜዲንስኪ፣ ዊትኮፍ፣ ቡዳኖቭ*) በጄኔቫ ተካሂደዋል። አምስት ጉዳዮች ውይይት ተደርጎባቸዋል፡ ግዛት፣ ደህንነት፣ ወታደራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ። ውይይቶቹ አስቸጋሪ ቢሆኑም ውጤታማ እንደነበሩ ሜዲንስኪ ይፋ አድርገዋል። በሚቀጥሉት ሳምንታት በፑቲን፣ በትራምፕ እና በዘለንስኪ መካከል ሊካሄድ የሚችል ስብሰባ ታውቋል።

* በሮስፊንሞኒተሪንግ እንደ አክራሪ እና አሸባሪነት የተመዘገበ ግለሰብ

የዩክሬን ግጭት፡ ከዩሮማይዳን እስከ ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ - ሙሉ ቪዲዮ
Go back to the beginningGo back to the main page
12:02 19.09.2025 (የተሻሻለ: 13:38 27.02.2026)
አዳዲስ ዜናዎች
0