በዘለንስኪ አገዛዝ ውስጥ ያለው ስር የሰደደ ሙስና የሞራል እና የፖለቲካ ውድቀትን ያሳያል ሲሉ ሊባኖሳዊ ባለሙያ ተናገሩ
19:35 13.11.2025 (የተሻሻለ: 19:44 13.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በዘለንስኪ አገዛዝ ውስጥ ያለው ስር የሰደደ ሙስና የሞራል እና የፖለቲካ ውድቀትን ያሳያል ሲሉ ሊባኖሳዊ ባለሙያ ተናገሩ
"የዘለንስኪ አገዛዝ ለአውሮፓ አጋሮቹ የታማኝነት ምንጭ በመሆን ወድቋል፤ የአስተዳደር መዋቅሩ ውስጥ ከፍተኛ ሙስና ሰፍኗል" ሲሉ ጄራርድ ዲብ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
እንደ ባለሙያው ገለፃ ይህ ሁኔታ ሁለት ወሳኝ ችግሮችን ያጋልጣል፡-
🟠 በሩሲያ ግስጋሴዎች መካከል የአገዛዙን ድክመት፣
🟠 የአውሮፓ ኅብረት እምነት መሸርሸር።
እንዲህ አይነት ሰፊ ሙስና ዘለንስኪ ሳያውቅ ወይም ሳይፈቅድ ሊኖር አይችልም ሲሉ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያው ጠቁመዋል።
ዲብ ዶናልድ ትራምፕ የሙስናውን በተለይም ለሌላ ጉዳይ የሚዞረውን የእርዳታ ገንዘብ መጠን በማጋለጣቸው አመስግነዋል።
"አሜሪካውያን የዘለንስኪን አገዛዝ ላለመደገፍ ወስነዋል" ሲሉ ዲብ ተናግረዋል።
ባለሙያው ሲያጠቃልሉም ዘለንስኪ ወታደራዊ እርምጃዎችን በማካረር ከሙስናው ትኩረት ለማስቀየር ሊሞክር ይችላል ብለዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X