ኢትዮጵያ የሕጻናት መብት እና ደህንነትን የሚያረጋግጡ ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነች ነው - የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ የሕጻናት መብት እና ደህንነትን የሚያረጋግጡ ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነች ነው - የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር

የሕጻናት ብሔራዊ ፖሊሲ አካላዊ እና አዕምሯዊ ጤናቸው የተጠበ ብቁ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት ከፍተኛ እገዛ እንዳለው በሚኒስቴሩ የሕፃናት ጥበቃ ከፍተኛ ባለሙያ ዮሐንስ አበባየሁ ይናገራሉ።

ስፑትኒክ አፍሪካ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ፖሊሲው የሕጻናትን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ እና በሕጻናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከል ልዩ ትኩረት መስጠቱን አንስተዋል።

"ሕፃናት ተገቢ በሆነ ሥርዓተ ምግብ፣ ትምህርት እና ጤና እንዲያድጉ እየሠራን ነው። የሕጻናት መዋያ፣ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች እና የምገባ መርሐ ግብሮችን ማስፋትም አበረታች ውጤቶች ተገኝቶባቸዋል" ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0