በአዲስ አበባ የኤሌክትሪክ አውቶብስ ፈጣን መስመር ግንባታ በሚቀጥለው ወር እንደሚጀመር ተገለፀ
17:03 13.11.2025 (የተሻሻለ: 17:04 13.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በአዲስ አበባ የኤሌክትሪክ አውቶብስ ፈጣን መስመር ግንባታ በሚቀጥለው ወር እንደሚጀመር ተገለፀ
በመዲናዋ የመጀመሪያ የሆነውና ከፒያሳ እስከ ጀሞ-3 ኮንዶሚኒየም የሚዘረጋው የኤሌክትሪክ አውቶቡስ ፈጣን መንገድ ኮሪደር ግንባታን በታህሳስ ወር ለማስጀመር መዘጋጀቱን የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡
15.64 ኪሎ ሜትር ሽፋን፣ 20 ዘመናዊ ጣቢያዎችን እና 12 ተጨማሪ አገልግሎቶችን የሚይዘው ይህ ፕሮጀክት፤ በሁለት ዓመት ግዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የባለሥልጣኑ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር እያሱ ሰለሞን ተናግረዋል፡፡
መንገዱ በቀን 400 ሺህ የሚደርሱ መንገደኞችን እንደሚያስተናግድ የሚጠበቅ ሲሆን ወጪው በከተማ አስተዳደሩ እና በአጋር ድርጅቶች ይሸፈናል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X