አፍሪካ ባሕላዊ የይዞታ መብቶችን ያከበረ የመሬት ምዝገባ ሥርዓት ያስፈልጋታል - ተመራማሪ

ሰብስክራይብ

አፍሪካ ባሕላዊ የይዞታ መብቶችን ያከበረ የመሬት ምዝገባ ሥርዓት ያስፈልጋታል - ተመራማሪ

የኬንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሀገሪቱ የመሬት ምዝገባ ባሕላዊ የይዞታ አሠራሮችን እንደማያስቀር ያሳለፈው ውሳኔ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አብነት መሆኑን በኬንያ ኢምቡ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና ተመራማሪው ዊልሰን ንጊጊ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልፀዋል፡፡

"ኬንያ ውስጥ ጥሩ ለውጦችን አይተናል። እኚህ ባሕላዊ መብቶች ከፀደቁ በምዝገባ ሊሰረዙ አይችሉም ማለት ነው። ይህም ተራማጅ እና አካታች ውሳኔ ሆኖ አግኝተነዋል" ብለዋል።

ተመራማሪው ውሳኔው በቅኝ ግዛት የመሬት አስተዳደር ሥርዓት የተወለዱ ማኅበራዊ ቀውሶችን ለማረም የላቀ እገዛ እንዳለውም አመላክተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0