‘በሽብርተኛው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሚሊሻ ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች መኖር አልተቻለም’ - አል-ቡርሃን

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ‘በሽብርተኛው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሚሊሻ ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች መኖር አልተቻለም’ - አል-ቡርሃን
‘በሽብርተኛው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሚሊሻ ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች መኖር አልተቻለም’ - አል-ቡርሃን - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.11.2025
ሰብስክራይብ

‘በሽብርተኛው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሚሊሻ ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች መኖር አልተቻለም’ - አል-ቡርሃን

የሱዳን የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤት መሪ ጄኔራል አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን በኤክስ ገፃቸው ላይ ባወጡት መግለጫ፤ መሀመድ ሃምዳን ዳጋሎ የሚመራው አማፂው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሚሊሻ በሚደርስበት ቦታ ሁሉ ሲቪሎች እየሸሹ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

"ከኤል-ፋሸር፣ ባራ እና አል-ኑሁድ በግዳጅ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ኒያላ፣ አል-ፉላ አልያም በሚሊሻ ቁጥጥር ስር ወዳሉ የዳርፉር እና የምዕራብ ኮርዶፋን ማንኛውም አካባቢዎች አልሄዱም" ብለዋል።

"ይልቁንም በሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን በእግር መጓዝን ምርጫቸው በማድረግ ደህንነት እና ህይወታቸውን መግፋት ወደሚችሉባቸው በመንግሥት እና የመንግሥት ኃይሎች ቁጥጥር ስር ወደሚገኙ አካባቢዎች መሄድን መርጠዋል" ሲሉ መሪው አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0