ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኤርትራ ላይ ጫናዎችን እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኤርትራ ላይ ጫናዎችን እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበች
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኤርትራ ላይ ጫናዎችን እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.11.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኤርትራ ላይ ጫናዎችን እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበች

ጥሪው የቀረበው ትኩረቱን በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ ባሉ ወቅታዊ ተለዋዋጭ የፖለቲካና የደህንነት ሁነቶች ላይ አድርጎ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመካሄድ ላይ ባለው የውይይት መድረክ ነው።

ከጥቂት ዓመታት በፊት ተሻሽሎ የነበረው የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ግንኙነት በአስመራው መንግሥት ጸብ አጫሪ ድርጊቶችና ትንኮሳዎች ምክንያት እየሻከረ መምጣቱን ስብሰባውን የከፈቱት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ገልጸዋል ሲል የስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ ዘግቧል።

በተለይ ኢትዮጵያ የወደብና የባሕር በር ጥያቄዎችን ማንሳቷን ተከትሎ ከኤርትራ መንግሥት ጋር ያለው ግንኙነት የበለጠ መሻከሩን በማንሳት፤ የኤርትራ መንግሥት የኢትዮጵያን ሰላም ለማደፍረስና እድገቷን ለማደናቀፍ ታጣቂዎችን ከመደገፍና ከማስታጠቅ ጀምሮ ዐይነተ ብዙ ትንኮሳዎች እያደረገ እና የውጭ አካላት ወኪል ሆኖ እያገለገለ ይገኛል ብለዋል።

"በሉዓላዊነታችንና በብሔራዊ ጥቅማችን እየተቃጣ ለሚገኘው ጣልቃ ገብነት የአጸፋ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል በቂ ምክንያት ቢኖረንም ሁኔታውን በትዕግስት መከታተልን መርጠናል" ሲሉም ተናግረዋል።

በሀገራቱ መካከል የተፈጠረው የተካረረ ቅራኔ ምጣኔ ሀብትን ጨምሮ በሌሎችም ዘርፎች ሊደረጉ በሚችሉ የሁለትዮሽና ቀጣናዊ ትብብሮች ሊፈታ እንደሚችልም ገልጸው፤ ሁለቱም ሀገራት ይህን ለማሳካት የሚያስችል ደማዊና ታሪካዊ ጥብቅ ግንኙነት እንዳላቸው አብራርተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኤርትራ ላይ ጫናዎችን እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበች - Sputnik አፍሪካ
1/3
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኤርትራ ላይ ጫናዎችን እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበች - Sputnik አፍሪካ
2/3
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኤርትራ ላይ ጫናዎችን እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበች - Sputnik አፍሪካ
3/3
1/3
2/3
3/3
አዳዲስ ዜናዎች
0