የሩሲያ እና ዩክሬን ሶስተኛ ዙር የድርድር ቀን በሚቀጥለው ሳምንት ይወሰናል ተብሎ እንደሚጠብቅ ክሬምሊን ገለፀ
11:49 20.06.2025 (የተሻሻለ: 12:04 20.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ እና ዩክሬን ሶስተኛ ዙር የድርድር ቀን በሚቀጥለው ሳምንት ይወሰናል ተብሎ እንደሚጠብቅ ክሬምሊን ገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ እና ዩክሬን ሶስተኛ ዙር የድርድር ቀን በሚቀጥለው ሳምንት ይወሰናል ተብሎ እንደሚጠብቅ ክሬምሊን ገለፀ
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለዩናይትድ ኪንግደም ብሮድካስተር እንደተናገሩት "ምን እንደሚፈጠር ወደፊት የምናየው ይሆናል። በእርቀ ሰላም ረቂቆች ላይ የጋራ ምላሻችንን መለዋወጥ ይኖርብናል" ብለዋል።
ባለሥልጣኑ አክለውም ሞስኮ ከኪዬቭ ጋር የሚደረገውን ድርድር በከፍተኛ ሁኔታ እንደምትመለከተው ገልጸዋል፡፡
ፔስኮቭ ቀጣዩ ዙር ድርድር የሚደረግበት ቀን በጋራ እንደሚወሰን ለስፑትኒክ ተናግረዋል፡፡
በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል የተደረገው ሁለተኛው ዙር የሰላም ውይይት ግንቦት 25 በቱርክ ተካሂዷል። በስብሰባው ላይ ሁለቱ ወገኖች የግጭቱን አፈታት በሚመለከት የመግባቢያ ሰነዶችን የተለዋወጡ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በመካሄድ ላይ ባለው መጠነ ሰፊ የጦር ምርኮኞች ልውውጥ ላይም ተስማምተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X