ብራዚል እና ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ስር የግብርና ትብብራቸውን እያሳደጉ ነው ተባለ
11:05 20.06.2025 (የተሻሻለ: 11:24 20.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ብራዚል እና ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ስር የግብርና ትብብራቸውን እያሳደጉ ነው ተባለ
ከአንድ ወር በፊት በኢትዮጵያ እና በብራዚል መካከል የተፈረመው የግብርና ትብብር ስምምነት የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር እና የጋራ ምርምርን ለማበረታታት ያለመና በብሪክስ ማዕቀፍ ያለውን ሰፊ ትብብር የሚያንፀባርቅ እንደሆነ በኢትዮጵያ የብራዚል ኤምባሲ የግብርና ጉዳዮች ኃላፊ ፋቢያና ቪላ አልቬስ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ብራዚል በግብርና ላይ የተመሠረተውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የሞቃታማ አካባቢዎችን ምርታማነትን የሚያጎለብቱ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማጋራት ልታግዝ እንደምትችል ገልፀዋል፡፡
አልቬስ የኢትዮጵያን የቅርብ ጊዜ እድገት እና የብሪክስ አባልነት በማውሳት፤ የብራዚልን ዘላቂ ትብብር የማጎልበት ፍላጎት ገልጸዋል።
አክለውም በተለይ ሻንጋይ መቀመጫውን ያደረገው የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክ የዓለምን ረሃብ በመዋጋት ረገድ ወሳኝ ሚና ሊጫወት እንደሚችል ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X