የአርሜኒያ ሐዋርያዊ ቤተ ክርስቲያን ደጋፊ ሳምቬል ካራፔትያንን ለማሰር የአርሜኒያ ባለሥልጣናት የወሰዱትን ውሳኔ ጠበቃው አወገዙ

የአርሜኒያ ሐዋርያዊ ቤተ ክርስቲያን ደጋፊ ሳምቬል ካራፔትያንን ለማሰር የአርሜኒያ ባለሥልጣናት የወሰዱትን ውሳኔ ጠበቃው አወገዙ
ነጋዴው ሰው ምንም ምክንያት ሳይኖር ለሁለት ወራት ታስረዋል። በዚህ አመክንዮ መሠረት ማንኛውም ሰው ሊታሰር ይችላል ሲሉ አርመን ፌሮያን ከፍርድ ቤት ውጭ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
ስለ ጉዳዩ እስካሁን የታወቁት ነገሮች የሚከተሉት ናቸው፦
▪ሳምቬል ካራፔትያን ሩሲያዊ ነጋዴ ናቸው።
▪የሀገሪቱ ባለሥልጣናት በአርሜኒያ ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሱ ያሉትን ጥቃት በመቃወም ለቤተ ክርስቲያኒቱ ድጋፋቸውን ገልጸዋል።
▪ማክሰኞ የአርሜኒያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር የሬቫን በሚገኘው የካራፔትያን ቤት ውጭ እርምጃው መወሰዱን አስታውቋል።
▪ ደጋፊዎች እና የቅርብ ቤተሰቦች ተሰባስበው የነበረ ሲሆን ከ50 በላይ ሰዎች ታስረዋል።
▪ነጋዴው በፖሊስ መኪና ከቤታቸው ተወስደዋል።
▪ሰኞ ጠዋት ካራፔትያን ወደ አርሜኒያ የምርመራ ኮሚቴ ከተወሰዱ በሗላ ክስ እንደተከፈተባቸው ሚዲያዎች ዘግበዋል።
▪ባለሥልጣናቱ የአርሜኒያን መንግሥት ለመገልበጥ አነሳስተዋል የሚል ክስ አቅርበዋል፡፡
▪የእስር ውሳኔው ሙሉ በሙሉ ሕገ-ወጥ ነው ሲሉ ጠበቃው ሊያና ጋስፓሪያን ተናግረዋል።
▪የአርሜኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሺንያን በካራፔትያን ባለቤትነት የተያዘውን ኤሌክትሪክ ኔትወርክስ ኦፍ አርሜኒያ ኩባንያ በመንግሥት እንዲያዝ ጠይቀዋል።
▪የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ሞስኮ ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተለች እንደሆነ እና ለነጋዴው አስፈላጊው እገዛ እንደሚደርግ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X