ለኢራን የ 'ጦርነት ወይም ድርድር' አማራጭ ተቀባይነት የለውም - የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ

© telegram sputnik_ethiopiaለኢራን የ 'ጦርነት ወይም ድርድር' አማራጭ ተቀባይነት የለውም - የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ
ለኢራን የ 'ጦርነት ወይም ድርድር' አማራጭ ተቀባይነት የለውም - የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.09.2026
ሰብስክራይብ

ለኢራን የ 'ጦርነት ወይም ድርድር' አማራጭ ተቀባይነት የለውም - የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ

"አንድ አካል እየተዋጋ መደራደርም ስለሚኖርበት 'የጦርነት ወይም ድርድር' አማራጭ የተሳሳተ ነው ብለን እናምናለን" ሲሉ መሐመድ- ባገር ጋሊባፍ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።

አፈ-ጉባኤው በመግለጫቸው  ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦

ኢራን ጠንካራ አቋም በመያዝ በጥበብ መዋጋት እና በትክክለኛው ጊዜ መደራደር አለባት፣

ይህ ጊዜው ሲመች ባለን ወታደራዊ አቅም ሁሉ ጠላትን መመከት እና አንበርካኪ ምት ማሳረፍ ማለት ነው፣

በውጊያው ጉልህ ድል ካስመዘገብን እና ጠላትን ካዳከምን በኋላ ያገኘነውን ስኬት ለማጠናከር፣ አቋማችንን ለማጎልበት እና አለመደፈራችንን ለማረጋገጥ ዲፕሎማሲን መጠቀም አለብን፣

ወቅታዊ የዲፕሎማሲ አቋማችን ሙሉ በሙሉ ግልጽ፣ ምክንያታዊ እና ለድርድር የማይቀርብ ነው፣

ቅድመ ሁኔታዎቻችንን በአሸማጋዩቻችን በኩል በግልጽ ያሳወቅን ሲሆን ጠላትም ማታለል እና የአንድ ወገን ፍላጎት ከእንግዲህ ተቀባይነት እንደሌለው ተገንዝቧል፣

እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎች እስካልተሟሉ፣ የኢራን ሕጋዊ መብቶች እስካልተከበሩ እና አሜሪካ ገብታ የነበረችውን ቃል እስካልፈጸመች ድረስ፤ ወደ ድርድር መመለስም ሆነ የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ መከፈት አይታሰብም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0