የጎሪላዎች ቁጥር መጨመሩን ተከትሎ የኡጋንዳ የጎሪላ ቱሪዝም ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን የሀገሪቱ የዱር እንስሳት ባለሥልጣን አስታወቀ

ሰብስክራይብ

የጎሪላዎች ቁጥር መጨመሩን ተከትሎ የኡጋንዳ የጎሪላ ቱሪዝም ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን የሀገሪቱ የዱር እንስሳት ባለሥልጣን አስታወቀ

​የኡጋንዳ የጎሪላ ቱሪዝም ገቢ ከ2023/24 22 ሚሊዮን ዶላር በ2025/26 የበጀት ዓመት ወደ 28 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ከፍ ማለቱን የኡጋንዳ የዱር እንስሳት ባለሥልጣን አስታውቋል።

​ በተከታታይ በተካሄዱ የቱሪዝም ማስተዋወቅ ዘመቻዎች በመታገዝ የመጣው ይህ ዕድገት፤ በአጠቃላይ የ41 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አስተዋጽኦ ማድረጉን የኡጋንዳ የዱር እንስሳት ባለሥልጣን የብዝሃ ሕይወት አስተዳደር ኮሚሽነር ጆን ማኮምቦ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል።

​የገቢው እድገት በአዳዲስ መራባቶች ምክንያት ከመጣው የተራራ ጎሪላዎች ቁጥር መጨመር ጋር የተያያዘ መሆኑንም ጠቁመዋል።

​ℹ ኡጋንዳ በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ ከሚገኙት የተራራ ላጎሪላዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት መገኛ ስትሆን፤ በግንቦት 2025 የተጀመረው አዲስ ቆጠራ የመጨረሻ የዲኤንኤ ትንተና ውጤት እየተጠበቀ ይገኛል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0