የዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ የሠራተኞቹን ቁጥር እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2029 በእጥፍ ለማሳደግ አቀደ

ሰብስክራይብ

የዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ የሠራተኞቹን ቁጥር እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2029 በእጥፍ ለማሳደግ አቀደ

የአፍሪካ ትልቁ የነዳጅ ማጣሪያ የምርት ማስፋፊያ ሥራውን ለመደገፍ እስከ እ.ኤ.አ 2029 ድረስ የሠራተኞቹን ቁጥር በእጥፍ ለማሳደግ ማቀዱን የዳንጎቴ ኢንዱስትሪ ምክትል ፕሬዝዳንት ዴቫኩማር ኤድዊንን ጠቅሰው የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

“በማጣሪያው ውስጥ ያለው የሠራተኞች ቁጥር በውኃ ማጣሪያ ክፍል ካለው በስተቀር በተግባር እጥፍ ይሆናል። ምክንያቱም በዚያ ክፍል አስቀድሞ በቂ አቅም አለን” ብለዋል።

በአጭር ጊዜ ውስጥ በትራንስፖርት ዘርፍ ተጨማሪ ሠራተኞችን የመቅጠር ሁኔታ የሚፈጠረው የሀገር ውስጥ የነዳጅ ፍላጎት ካደገ ብቻ መሆኑን ኤድዊን ጨምረው አብራርተዋል።

  በቅርቡ ማጣሪያው ለተጨማሪ ማስፋፊያ የሚሆን ወደ 1.6 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ለማሰባሰብ ያለመ የመጀመሪያ ደረጃ የአክሲዮን ሽያጭ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0