የምዕራባውያን ቅኝ አገዛዝና የባሪያ ንግድ በአፍሪካውያና በዲያስፖራው ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ አሁንም ቀጥሏል - የባሃማስ የካሳ ኮሚቴ ተባባሪ ሊቀመንበር

ሰብስክራይብ

የምዕራባውያን ቅኝ አገዛዝና የባሪያ ንግድ በአፍሪካውያና በዲያስፖራው ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ አሁንም ቀጥሏል - የባሃማስ የካሳ ኮሚቴ ተባባሪ ሊቀመንበር

በታሪክ፣ የማካካሻ ፍትሕ እና የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎች ላይ ያተኮረ ዓለም አቀፍ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ከኢትዮጵያ፣ ከባሃማስ፣ ከአፍሪካ፣ ከካሪቢያን፣ ከደቡባዊው ክፍለ ዓለም እና ከዲያስፖራ የተወጣጡ ድምፆች ምክክር እያደረጉ እንደሆነ የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ ዘግቧል።

የባሃማስ ብሔራዊ የማካካሻ ፍትሕ ኮሚቴ ተባባሪ ሊቀመንበር ፊሊፕ ስሚዝ፤ የአፍሪካ እና የካሪቢያን ሀገራት አሁንም ድረስ ዘልቆ የዘለቀውን የቅኝ ግዛት ውርስ በማስወገድ በራስ የመወሰን መብታቸውን ለማረጋገጥ በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።

"እውነተኛ ነፃነት የሚገኘው የአፍሪካ እና የዲያስፖራ ማኅበረሰቦች ለራሳቸው ዋጋ ሲሰጡ፣ የአእምሮ ባርነትን ሲቃወሙ እና የውስጥ ታላቅነታቸውን ነፃ ሲያወጡ ነው" ሲሉም አክለዋል።

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0