ፈጠራ እኩልነትን ከሚያጸኑ መሣሪያዎች መካከል ወሳኙ ነው - ደቡብ አፍሪካዊ የፈጠራ ባለቤት

ሰብስክራይብ

ፈጠራ እኩልነትን ከሚያጸኑ መሣሪያዎች መካከል ወሳኙ ነው - ደቡብ አፍሪካዊ የፈጠራ ባለቤት

 

"የሰዎች ዝውውር እና ሌሎች ማኅበራዊ ችግሮችን መቀነስ የሚችል መፍትሔ ለመፍጠር ኃላፊነቱን ወስጄ እሠራለሁ" ስትል በ16 ዓመቷ ሴቶችን ከጥቃት ለመጠበቅ የሚረዳ የአደጋ ጊዜ ጥሪ ቁልፍ ያላቸው የጆሮ ጌጦችን የሠራችው ቦህላሌ ምፋህሌሌ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግራለች።

የፈጠራ ሥራው በደቡብ አፍሪካ ትልቁ የትምህርት ቤቶች የሳይንስ ኤግዚቢሽን "የኤስኮም ኤክስፖ" የነሐስ ሜዳሊያ አስገኝቶላታል። እውቅናውን "ትልቅ ማረጋገጫ ያገኘሁበት" ነበር ስትል ታስታውሰዋለች።

ከሀገሪቷ ገጠራማ ስፍራ የመጣችውና የሀብት እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ እጥረት የነበረባት ምፋህሌሌ፤ "ብዙ ነገር አልነበረኝም፤ ነገር ግን ማንንም ላለመጠበቅ ወሰንኩ" ስትል አብራርታለች።

 

አሁን "ለመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጠሁ ነው፤ ይህም ኅብረተሰቡን ለማገልገል የምሞክርበት የእራሴ መንገድ ነው" ብላለች።

 

ይህ የፈጠራ ሥራ በተለይም በደቡብ አፍሪካ ሴቶችን ኢላማ አድርጎ እየተፈጸመ ባለው ተከታታይ ግድያ ወቅት ጠቀሜታው ከፍተኛ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0