ኒጀር የአምስት ግለሰቦችን ዜግነት በጊዜያዊነት ሰረዘች
16:00 18.09.2026 (የተሻሻለ: 16:04 18.09.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኒጀር የአምስት ግለሰቦችን ዜግነት በጊዜያዊነት ሰረዘች
ይህንን ውሳኔ የያዘው አዋጅ በኒጀር መሪ አብዱራሃማን ትያኒ መፈረሙን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ግለሰቦቹ በሚከተሉት ወንጀሎች ተከሰዋል፦
የሕዝብን ሰላምና ፀጥታ ሊያደፈርስ የሚችል መረጃ ማሰራጨት፣
ከውጭ ኃይሎች ጋር ማሴር፣
በኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ዘዴዎች ስም ማጥፋት፣
የሀገርን የመከላከል አቅም እና ማኅበራዊ አንድነትን ለመጎዳት የሠራዊቱን እና ሕዝቡን ሞራል የሚያዳክም ዘመቻ ላይ መሳተፍ፣
የሀገርን ደህንነት ማወክ።
የወንጀሉ ተጠቂ ከሆኑ ግለሰቦች መካከል በቀድሞው ፕሬዚዳንት ሞሃመድ ባዙም አስተዳደር በጠቅላይ ሚኒስትርነት ያገለገሉት ኦሁሙዱ ማሃማዱ እንደሚገኙበት ተገልጿል።
አዲሱ አዋጅ ዜግነታቸውን በጊዜያዊነት የተነፈጉ ግለሰቦችን ቁጥር ወደ 25 ያደርሰዋል። እርምጃው እ.ኤ.አ በ2024 በአሸባሪነት ተግባራት ወይም በሀገር ጥቅም ላይ ጉዳት በሚያደርሱ ድርጊቶች የተሳተፉ ሰዎችን ለመከታተል የተዘረጋውን መዝገብ ተከተሎ የተወሰደ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X