የሳኅል ሀገራት ጥምረት ከተመሠረተ ጀምሮ ምን ለውጦች አምጥቷል? የባለሙያዎችና የዜጎች ምላሽ
10:38 18.09.2026 (የተሻሻለ: 10:44 18.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሳኅል ሀገራት ጥምረት ከተመሠረተ ጀምሮ ምን ለውጦች አምጥቷል? የባለሙያዎችና የዜጎች ምላሽ
እ.ኤ.አ መስከረም 16 ቀን 2023 የተፈረመው የሊፕታኮ-ጉርማ ቻርተር የቡርኪና ፋሶ፣ የማሊ እና የኒጀር ጥምረት እንዲፈጠር እንዲሁም በሂደት ወደ ኮንፌዴሬሽን እንዲሸጋገር ትልቅ መነሻ ሆኗል።
የሳኅል ሀገራት ጥምረት በተለይም በመከላከያ፣ በደህንነት እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ትልቅ "ስኬት" አስመዝግቧል የሚሉት የማሊ የግንኙነት፣ የጦማሪዎች እና ሙያተኛ ተሟጋቾች ኔትወርክ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዲያሎ ናቸው።
ኢኮዋስ ከ ኤኢኤስ
የማሊው 'ሌ ትሪዮምፍ' ጋዜጣ የህትመት ዳይሬክተር ባዱ ኤስ. ኮባ፤ "ኢኮዋስ በሳኀል ቀጠና ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ሙሉ በሙሉ አልተጋም" ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።
በኮንፌዴሬሽኑ እና በምዕራባውያን መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው?
ምዕራባውያን "እኛን ለመቆጣጠር ሁልጊዜም 'ከፋፍለህ ግዛ' ፖሊሲ ሲተገብሩ"፤ ኤኢኤስ ግን "ኅብረት ጥንካሬ ነው" የሚለውን መርህ ያበረታታል ሲል ዜጋ ሀምዛ ዲያሎ ተናግሯል።
ሞሃመድ ትራኦሬ የተባሉ ማሊያዊ የጭነት መኪና አሽከርካሪ በበኩላቸው፤ "የተዋሃደ ሠራዊት የመመስረት እቅድ የሚደነቅ ነው" ብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X