ቡሩንዲ እና የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና፦ ተግዳሮቶች እና መፍትሔዎቹ ምንድናቸው?
10:10 18.09.2026 (የተሻሻለ: 10:14 18.09.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ቡሩንዲ እና የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና፦ ተግዳሮቶች እና መፍትሔዎቹ ምንድናቸው?
በቡሩንዲ የኢኮኖሚ ጉባኤ በዚህ ርዕስ ዙሪያ የተካሄደው የፓነል ውይይት ሞቅ ያለ ክርክር አስነስቷል።
በቦታው የተገኘው የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ እንደዘገበው፤ ተሳታፊዎቹ ለእውነተኛ ነፃ ንግድ ገና በርካታ እንቅፋቶች እንዳሉ አንስተው የሚከተሉን በማሳያነት ጠቅሰዋል፦
▪ የውጭ ንግድን ዕድሎችን የሚገድብ የምግብ ዋስትና እጦት፣
▪ አምራቾች ምርቶቻቸውን በትክክል መሸጥ አለመቻላቸው፣
▪ ለደረጃዎችና ጥራት ማረጋገጫ በቂ ትኩረት አለመስጠት፣
▪ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት የሚያስተባብር ስትራቴጂ አለመኖር፣
▪ ለሰደድ እሳት አደጋ የመጋለጥ ከፍተኛ ስጋት።
ሀገሪቱ "የፋይናንስ አቅርቦትን ለማመቻቸት" የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ እንዲሁም "መድህን ሰጪዎች ተጨማሪ ስጋቶችን እንዲሸፍኑ" የሚያሳምኑ ሁኔታዎች ያስፈልጓታል ሲሉም ተከራክረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X