ዓለም አቀፍ ጫናዎች ቢኖሩም የሩሲያ ኢኮኖሚ መረጋጋቱን አስጠብቋል - ፑቲን

ሰብስክራይብ

ዓለም አቀፍ ጫናዎች ቢኖሩም የሩሲያ ኢኮኖሚ መረጋጋቱን አስጠብቋል - ፑቲን

የሩሲያ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በቅድሚያ ግምቶች መሠረት እያደገ መሆኑን ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ በተካሄደ ስብሰባ ላይ ተናግረዋል። ኢኮኖሚው አነስተኛ የሥራ አጥነት ምጣኔ፣ የደመወዝ ዕድገት እና ከነዳጅ ውጪ የሆኑ ገቢዎች ጭማሪ እንዳስመዘገበ አንስተዋል።

ቁልፍ መግለጫዎች፦

በ2026 የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት 1% አካባቢ ሆኖ እንደሚቀጥል ይጠበቃል፣

በሩሲያ የሥራ አጥነት ምጣኔ በታሪክ ዝቅተኛ ወደሚባልበት ደረጃ በመድረስ 2.3% ሆኗል፣

የውጭ ጫናዎች ቢኖሩም የሩሲያ የንግድ ተቋማት በተረጋጋ ሁኔታ ሥራቸውን ማከናወናቸውን ቀጥለዋል፣

በ2026 የመጀመሪያ አጋማሽ የሠራተኞች ተጨባጭ የደመወዝ መጠን በ6.5% ጨምሯል፣

እ.አ.አ እስከ መስከረም 14 ባለው መረጃ ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት 6.4% ላይ ቆሟል፣

በነሐሴ ወር የፌዴራል በጀት የ606 ቢሊዮን ሩብል (7.2 ቢሊዮን ዶላር) ትርፍ አስመዝግቧል፣

ከነዳጅ እና ጋዝ ውጪ ያሉ ገቢዎች ለበጀቱ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያበረከቱ ሲሆን በዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት ውስጥ ከ18% በላይ ጭማሪ አሳይተዋል፣

የሩሲያ የሦስት ዓመት የፌዴራል በጀት ዕቅድ ዝግጅት ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0