ሊባኖስ በ2020 በቁጥጥር ስር ያዋለቻቸውን 37 የፈርኦን ዘመን ቅርሶች ለግብፅ አስረከበች

ሰብስክራይብ

ሊባኖስ በ2020 በቁጥጥር ስር ያዋለቻቸውን 37 የፈርኦን ዘመን ቅርሶች ለግብፅ አስረከበች

ከግብፅ በሕገ-ወጥ መንገድ ወጥተው በቤሩት ወደብ በቁጥጥር ስር ለዋሉት ቅርሶች፤ የሊባኖስ የባሕል ሚኒስትር ጊሳን ሳላመህ እና የግብፅ አምባሳደር አላህ ሙሳ በተገኙበት በቤሩት ብሔራዊ ሙዚየም በተካሄደ ሥነ-ሥርዓት ርክክብ መደረጉን የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች አመልክተዋል።

ቅርሶቹ የሚከተሉትን ያካትታሉ፡-

ሁለት የተቀቡ የእንጨት የሬሳ ሣጥኖች፣

የፊት ጭንብሎች እና የእንጨት ምስሎች፣

የኮፕቲክ ጨርቃጨርቆች፣

ከብርጭቆ ድብልቅ የተሠሩ የአንገት ክታቦች፣

መካከለኛ መጠን ያላቸው ሐውልቶች።

እንደ ሚኒስትር ሳላመህ ገለጻ፤ ቅርሶቹን የመመለስ ሂደት የተከናወነው የባሕላዊ ንብረቶችን ሕገ-ወጥ ዝውውር ለመግታት እ.ኤ.አ 1970 በወጣው ዓለም አቀፍ ስምምነት መሠረት ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0